በካቡል አውሮፕላን ማረፊያ ከ70 በላይ የአፍጋን ሰላማዊ ሰዎችና የዩናይትድ ስቴትስ ወታደሮች ተገደሉ

*** ፕሬዚደንት ባይደን "ይቅር አንልም፤ አንረሳምም" ሲሉ ጥቃት ፈጻሚዎችን አስጠነቀቁ

Jo Biden

U.S. President Joe Biden speaks about the situation in Kabul, Afghanistan from the East Room of the White House on August 26, 2021 in Washington, DC. Source: Getty

በሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች በተሰነዘረ የቦምብ ጥቃት 12 የዩናይትድ ስቴትስ ወታደሮችን ጨምሮ በታሊባን ቁጥጥር ስር የወደቀችውን አፍጋኒስታንን ለቅቀው ለመውጣት ካቡል አውሮፕላን ማረፊያ ዙሪያ ተሰባስበው የነበሩ 70 ሰላማዊ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።

ጥቃቱ የተፈጸመው በካቡል ሰዓት አቆጣጠር ሐሙስ ከቀትር በኋላ ሲሆን 143 ያህል ሰዎችም ቆስለዋል። 

ጥቃቱን አስመልክቶም እስላማዊ ስቴት ኬሆራሳን (ISIS-K) የተባለው ቡድን ኃላፊነቱን ወስዷል። እርምጃውንም የወሰደው "በአስተርጓሚዎችና የአሜሪካን ጦር ተባባሪዎች" ላይ እንደሆነ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። 

ጥቃቱን አስመልክቶ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ጆ ባይደን በሰጡት መግለጫ ድርጊቱ ጦራቸውን፣ ዜጎቻቸውንና ባለ ቪዛዎችን እስከ ኦገስት 31 ከማጓጓዝ እንደማያግዳቸው አስታውቀዋል። 

አክለውም ዩናይትድ ስቴትስ የበቀል እርምጃ እንደምትወስድ ሲያስጠነቅቁ "ይቅር አንልም፤ አንረሳምም። አድነን አፀፋውን እናስከፍላችኋለን" ብለዋል። ሕይወታቸውን ያጡትን የዩናይትድ ስቴትስ ወታደሮችም "ጀግኖች" ብለው አወድሰዋቸዋል። 

ክክስተቱ ጋር በተያያዘም አፍጋኒስታን የሚገኙ የአፍጋኒስታንያውያን-አውስትራሊያውያንን ሁኔታ አስመልክቶ ለጊዜው ይህ ይሆናል ለማለት እንደሚያውክ የአውስትራሊያ መከላከያ ሚኒስትር ፒታር ዳተን ተናግረዋል። 

አውስትራሊያ በስምንት ቀናት ውስጥ 4000 ሰዎችን ከአፍጋኒስታን ያስወጣች ሲሆን ሁሉም የአውስትራሊያ ወታደሮች ለቅቀው ወጥተዋል።   


1 min read

Published

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now