የሕወሓት ቡድን እንደ ኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከለሊቱ 7:40 ግድም የሮኪርት ጥቃት ማድረሱን አብመድ ዘግቧል።
በጥቃቱም በከተማይቱ ላይ ምንም የደረሰ ጉዳት እንደሌለ በክልሉ ባለ ስልጣናት ተገልጧል።
ባለፈው ሳምንት በጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ላይ በሕወሓት የሮኬት ጥቃት ደርሶ በባሕር ዳር አውሮፕላን አካባቢ ጉዳት ደርሷል።
በወቅቱም የሕወሓት ቃል አቀባይ ድርጊቱን በሁለቱ ከተሞችና በኤርትራ መዲና አሥመራም በድርጅታቸው ተዋጊ ኃይላት መፈጸሙን ተናግረዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ ሕወሓት በፌስቡክ ገጹ በመቀሌ መለስ ዜናዊ አካዳሚ ተማሪዎችና ሰላማዊ ሰዎች ላይ የፌዴራል መንግሥቱ አየር ኃይል በሰነዘረው የአየር ጥቃት መቁሰላቸውን አስታውቋል።
የድርጅቱ መሪ ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤልም መቀሌ ለአራተኛ ጊዜ የአየር ጥቃት የደረሰባት መሆኑን ገልጸዋል።
በፌዴራል መንግሥቱ በኩል በርካታ ከተሞችን ከሕወሓት እጅ አላቅቆ ወደ መቀሌ እያመራ መሆኑ ተነግሯል።

