ዩናይትድ ስቴትስ በኢትዮጵያና ሕወሓት መካከል የተደረሰውን የሰላም ስምምነት በማለፊያ ጎኑ መቀበሏን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ኅበረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ፋኪን፣ የአሸማጋይ ልዑክ ቡድን አባላትን፣ የደቡብ አፍሪካ መንግሥትን፣ ተመድና ኢጋድን፤ ሌሎችንም ሁለቱ ወገኖች ከስምምነት ላይ ለመድረስ እንዲችሉ ላስተባበሩ፣ እገዛ ላደረጉና ለተሳተፉ ተቋማት እንዲሁም፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን አክላ ምስጋና አቅርባለች።

SAFRICA ETHIOPIA TIGRAY UNREST CONFLICT PEACE TALKS.jpg

Kenyan President Uhuru Kenyatta (L), Redwan Hussein (2nd L), Representative of the Ethiopian government, African Union Horn of Africa envoy and former Nigerian president Olusegun Obasanjo (2nd R), and Getachew Reda (R), Representative of the Tigray People's Liberation Front (TPLF), look on after the signing of a peace agreement during a press conference regarding the African Union-led negotiations to resolve conflict in Ethiopia at the Department of International Relations and Cooperation (DIRCO) offices in Pretoria on November 2, 2022. Credit: PHILL MAGAKOE/AFP via Getty Images

ዩናይትድ ስቴትስ ትናንት ረቡዕ ጥቅምት 23 ፕሪቶሪያ - ደቡብ አፍሪካ ውስጥ በኢትዮጵያ መንግሥትና ሕወሓት መካከል "ጠብመንጃዎችን ፀጥ" ለማሰኘት የተደረሰውን የሰላም ስምምነት በመልካም ጎኑ መቀበሏን በመግለጫዋ አስታወቀች።

የሰላም ስምምነቱን አስመልክቶ መግለጫውን ይፋ ያደረገው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሁለቱም ወገኖች ግጭቱ እንዲቆም የወሰዱትን የስምምነት እርምጃ ተከትሎ የሁለት ዓመቱን ጦርነት ለመክላትና ሰላምን ለማስፈን በንግግራቸው እንዲቀጥሉ አበረታቷል።

ገደብ ያልተጣለባቸው የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦትና የሰላማዊ ሰዎች ደኅንነት ጥበቃ ግብር ላይ ለማዋል ከስምምነት ላይ መደረሱንም በማለፊያ ጎንነት ጠቅሷል።
ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የአፍሪካ ኅበረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ፋኪን፣ የአሸማጋይ ልዑክ ቡድን መሪ አባሳንጆን፣ የቡድኑ አባላትን ኡሁሩ ኬንያታና ምላምቦ ንግኩካ፣ የደቡብ አፍሪካ መንግሥትን፣ ተመድ፣ ኢጋድን አክሎ ሌሎችንም ሁለቱ ወገኖች ከስምምነት ላይ ለመድረስ እንዲችሉ ላስተባበሩ፣ እገዛ ላደረጉና ለተሳተፉ ተቋማት ሁሉ ምስጋናውን አቅርቧል።
አይይዞም፤ ዩናይትድ ስቴትስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለስምምነቱ ዳር መድረስ አስተዋፅ ላደረጉ አካላት ያቀረቡትን የምስጋና መግለጫ በመልካምነት መቀበሏን ገልጧል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል የሰላም ልዑክ ቡድን መሪ ሆነው በፕሪቶሪያ በመገኘት የሰላም ስምምነቱ ሰነድ ላይ ፊርማቸውን ያኖሩት የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ለመላ ኢትዮጵውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክታቸውን ገልጠዋል።
የሕወሓት የሰላም ልዑክ ቡድን መሪና ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ ግና እስካሁን በቲዊተር ገፃቸው ወይም በጋዜጣዊ መግለጫ ስምምነቱን አስመልክቶ ያሉት የለም።

ስምምነቱ ከተፈረመ 24 ሰዓታት አንስቶ ወደ ዝርዝር ትግበራ የሚያመራ ሲሆን፤ በሂደቱም በርካታ የተናጠልና የጋራ መግለጫዎች በይፋ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
ዩናይትድ ስቴትስ በኢትዮጵያና ሕወሓት መካከል የተደረሰውን የሰላም ስምምነት በማለፊያ ጎኑ መቀበሏን አስታወቀች | SBS Amharic