የቫይረስ ነጻ ማረጋገጫ መመሪያው ከ72 ሰዓታት ወደ አምስት ቀናት እንዲለወጥ የተደረገው በርካታ መንገደኞች ከመነሻቸው ወደ ኢትዮጵያ ለመዝለቅ ከ72 ሰዓታት በላይ እንደሚፈጅባቸው በመጥቀስ የማሻሻያ ጥያቄዎችን ማቅረብ ከግምት ውስጥ ገብቶ መሆኑን የጤና ሚንስትር ሊያ ታደሰ አስታውቀዋል።
ድንጋጌው ላይ ማሻሻያ ያደረገው የሚኒስትሮች ኮቪድ - 19 ኮሚቴ ነው።
በማሻሻያ ድንጋጌው ላይ የቴክኒክ ቡድኑም መክሮ ይሁንታውን የቸረ መሆኑ ተገልጧል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞም በአምስት ቀናት ውስጥ የኮሮናቫይረስ ነጻ ማረጋገጫ ያላቸው መንገደኞች አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ናሙና ሰጥተው ወደ አገር ከዘለቁ በኋላ ቀደም ሲል እንደነበረው ለ 14 ቀናት ወሸባ አይገቡም።
Share

