የአውስትራሊያ ማዕከላዊ ባንክ የዋጋ ግሽበትን ለመከላከል ለአራተኛ ጊዜ የወለድ መጠን ጭማሪ አደረገ

*** ለ25 ዓመታት የ $500,000 የቤት ብድር ያለባቸው ግለሰቦች በአራቱ ተከታታይ ተጨማሪ የወለድ መጠኖች ሳቢያ በወር $472 ተጨማሪ ክፍያ ለማድረግ ግድ ይሰኛሉ።

News

Throughout the pandemic, Australia's interest rate sat at 0.10 per cent, but that started to change from May this year. Source: SBS

የአውስትራሊያ ማዕከላዊ ባንክ የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ዛሬ ማክሰኞ ኦገስት 2 / ሐምሌ 26 የ1.85 ፐርሰንት ጭማሪ አድርጓል።

የዛሬው ጭማሪ የተደረገው ለአራተኛ ተከታታይ ጊዜ ነው።

የባንኩ ገዢ ፊሊፕ ሎዊ እርምጃው የአውስትራሊያን ፋይናንስ ሁኔታ ለማርጋት የተወሰደ ተጨማሪ እርምጃ እንደሆነ ገልጠዋል።  

እንደ ሬትሲቲ ስሌት ለ25 ዓመታት የ $500,000 የቤት ብድር ያለባቸው ግለሰቦች በአራቱ ተከታታይ ተጨማሪ የወለድ መጠኖች ሳቢያ በወር $472 ተጨማሪ ክፍያ ለማድረግ ግድ ይሰኛሉ።

የፌዴራል በጅሮንድ ጂም ቻልመርስ ዛሬ ፓርላማ ውስጥ ይህንኑ ጭማሪ አስመልክተው ሲናገሩ፤

"የቤት ብድራቸውን ለመክፈል ለሚጥሩ አውስትራሊያውያን አዋኪ ቀን ነው"

"ውሳኔው ለማንም ድንገተኛ አይደለም፣ አስደንጋጭም አይደለም። እንዲያም ሆኖ ግና ተናዳፊ ነው"ብለዋል።

አክለውም፤ ቤተሰቦች ዋጋቸው አሻቅበው ባሉት የግሮሰሪ፣ የነዳጅና ሌሎች ወጪዎች ጋር ለማቻቻል ጫና የበዛበት ውሳኔዎች ላይ ለመድረስ ግድ እንደሚሰኙ አመላክተዋል።  


1 min read

Published

Updated

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now