የአውስትራሊያ ማዕከላዊ ባንክ የዋጋ ግሽበትን ለመከላከል ለአራተኛ ጊዜ የወለድ መጠን ጭማሪ አደረገ

*** ለ25 ዓመታት የ $500,000 የቤት ብድር ያለባቸው ግለሰቦች በአራቱ ተከታታይ ተጨማሪ የወለድ መጠኖች ሳቢያ በወር $472 ተጨማሪ ክፍያ ለማድረግ ግድ ይሰኛሉ።

News

Throughout the pandemic, Australia's interest rate sat at 0.10 per cent, but that started to change from May this year. Source: SBS

የአውስትራሊያ ማዕከላዊ ባንክ የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ዛሬ ማክሰኞ ኦገስት 2 / ሐምሌ 26 የ1.85 ፐርሰንት ጭማሪ አድርጓል።

የዛሬው ጭማሪ የተደረገው ለአራተኛ ተከታታይ ጊዜ ነው።

የባንኩ ገዢ ፊሊፕ ሎዊ እርምጃው የአውስትራሊያን ፋይናንስ ሁኔታ ለማርጋት የተወሰደ ተጨማሪ እርምጃ እንደሆነ ገልጠዋል።  

እንደ ሬትሲቲ ስሌት ለ25 ዓመታት የ $500,000 የቤት ብድር ያለባቸው ግለሰቦች በአራቱ ተከታታይ ተጨማሪ የወለድ መጠኖች ሳቢያ በወር $472 ተጨማሪ ክፍያ ለማድረግ ግድ ይሰኛሉ።

የፌዴራል በጅሮንድ ጂም ቻልመርስ ዛሬ ፓርላማ ውስጥ ይህንኑ ጭማሪ አስመልክተው ሲናገሩ፤

"የቤት ብድራቸውን ለመክፈል ለሚጥሩ አውስትራሊያውያን አዋኪ ቀን ነው"

"ውሳኔው ለማንም ድንገተኛ አይደለም፣ አስደንጋጭም አይደለም። እንዲያም ሆኖ ግና ተናዳፊ ነው"ብለዋል።

አክለውም፤ ቤተሰቦች ዋጋቸው አሻቅበው ባሉት የግሮሰሪ፣ የነዳጅና ሌሎች ወጪዎች ጋር ለማቻቻል ጫና የበዛበት ውሳኔዎች ላይ ለመድረስ ግድ እንደሚሰኙ አመላክተዋል።  


Share

Published

Updated

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service