2.7 ሚሊየን ዝቅተኛ ተከፋይ አውስትራሊያውያን ከጁላይ አንድ አንስቶ በሳምንት የ47 ዶላር የደመወዝ ጭማሪ ማግኘት ይጀምራሉ።
ለ5.75 ፐርሰንት የደመወዝ ጭማሪው ይሁንታውን የቸረው የፍትሕ ሥራ ኮሚሽን ካካሔደው ብሔራዊ የደመወዝ ክለሳ ተነስቶ መሆኑን አስታውቋል።
የፌዴራል መንግሥቱ የጭማሪ መጠን ሳይጠቅስ እያሻቀበ ካለው የዋጋ ግሽበት አኳያ ለዝቅተኛ ደመወዝ ተከፋዮች የደመወዝ ጭማሪ እንዲደረግ ድጋፉን የቸረ ሲሆን፤ የአውስትራሊያ ሠራተኞች ምክር ቤት የ7 ፐርሰንት ጭማሪ ጥያቄ ቀርቦ ነበር።
ጭማሪው ከ4 ፐርሰንት እንዳያልፍ አሳስቦ የነበረው የአውስትራሊያ የንግድ ምክር ቤትና ኢንዱስትሪ የ 5.75 ፐርሰንት የደመወዝ ዕድገት አነስተኛ ንግዶችን ሊጎዳ ይችላል ሲል ቅሬታውን ገልጧል።

