በዘንድሮው የፋይናንስ ዓመት ወደ አውስትራሊያ የሚመጡ ባለ ክህሎት ሠራተኞች ቁጥር ወደ 195 ሺህ ከፍ እንዲል ተወሰነ

ዛሬ የሚያበቃው የሥራዎችና ክህሎቶች ጉባዔ አውስትራሊያን ገጥሞ ባለው የሠራተኞች እጥረት ቀውስ ላይ አተኩሮ ይወያያል

Prime Minister Anthony Albanese.jpg

Prime Minister Anthony Albanese at the Jobs and Skills Summit at Parliament House in Canberra, where the focus on its final day will be migration, and tackling labour shortages. Credit: AAP / Lucas Coch

የአልባኒዚ መንግሥት ትናንት ተጀምሮ ዛሬ በሚያበቃው የሁለት ቀናት አገር አቀፍ የሥራዎችና ክህሎቶች ጉባኤ በዘንድሮው የፋይናንስ ዓመት 195 ሺህ ባለ ክህሎት ሠራተኞችን ወደ አውስትራሊያ እንዲገቡ የሚያደርግ መሆኑን አስታወቀ።

ይህንን የሠራተኞች ጣራ ገደብ ይፋ ያደረጉት የአገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትር ክሌየር ኦኒል ናቸው።

ሚኒስትሯ በገለጣቸው ወቅት ለ2022 ተይዞ የነበረው 160 ሺህ የባለ ክህሎት ሠራተኞች ቁጥር ጣራ 35 ሺህ ተጨማሪ ቪዛዎችን በማከል ወደ 195 ሺህ ከፍ እንዲል የተደረገ መሆኑን ገልጠዋል።

Home Affairs Minister Clare O’Neil.jpg
Home Affairs Minister Clare O’Neil. Credit: AAP / MICK TSIKAS/AAPIMAGE

ተጨማሪው የቪዛ ፈቃድ በእጅጉ አውስትራሊያ የምትሻቸው በሺህዎች የሚቆጠሩ ነርሶች፣ መሐንዲሶችና ሠራተኞች ወደ አውስትራሊያ እንዲመጡ ዕድል ከፋችና ቀውስ ቀናሽ እንደሚሆን አመላክተዋል።

Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service