በፐርዝ ሰሜናዊ ምሥራቅ ክፍለ ከተሞች 71 ያህል ቤቶች በደን ቃጠሎ ጋይተዋል።
የውሮሉ አሳት የተነሳው ሰኞ ፌብሪዋሪ 1 ሲሆን ከ 8,000 ሔክታር መሬት በላይ አንድዷል።
የአካባቢው ባለ ስልጣናት እንደገለጹት ከሆነ ምንም እንኳ ትናንት ማምሻውን የአሳት አደጋ ተከላካዮች ብርቱ የቃጠሎ ሁኔታ ባይገጥማቸውም ተከስቶ ያለው ሁኔታ እስከ ሳምንቱ መጨረሻ ለሚያደርጉት እሳት የማጥፋት ተግባር እምብዛም አጋዥ አይደለም።
የእሳትና ድንገተኛ አደጋ አግለግሎቶች ኮሚሽነር ዳረን ክሌም እስካሁን አንድም የሰው ሕይወት እንዳልጠፋ ገልጠው፤ ሆኖም ተጨማሪ ንብረቶች ሊወድሙ እንደሚችሉ ተናግረዋል።
ቫይረስ ቪክቶሪያ
ቪክቶሪያ አንዳችም የማኅበረሰብ አባል በኮሮናቫይረስ ሳይጠቃ 28 ተከታታይ ቀናትን አስቆጥራለች፡፡
የጤና ሚኒስትር ማርቲን ፎሊ ይህ ቫይረሱ ከማሕበረሰቡ ውስጥ የተከላበት ቀን በመሆኑ ሁነኛ ቀን እንደሆነ ተናግረዋል።
ይሁንና ጊዜው ቸል መባያ አለመሆኑንንም ልብ አሰኝተዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ የኒው ሳውዝ ዌይልስ ፕሪሚየር ግላዲስ በርጂክሊያን አንዳች ግዙፍ ለውጥ ካልተከሰተ በስተቀር በሚቀጥለው ሳምንት ፌብሪዋሪ 12 ላይ ተጥለው ያሉ ገደቦችን እንደሚያላሉ አስታውቀዋል።
ኒው ሳዝ ዌይልስ አንዳችም የማኅበረሰብ አባል በኮሮናቫይረስ ሳይጠቃ 17 ተከታታይ ቀናትን አስቆጥራለች፡፡

