በመላ አውስትራሊያ የሀገር አቀፍ ምርጫ ጣቢያዎች ተዘጉ፤ የድምፅ ቆጠራ ተጀመረ

የተቃዋሚ ቡድኑ አብላጫ ድምፅ አግኝቶ የማሸነፍ ዕድል እንደሌለውና መሪው ፒተር ዳተን የምክር ቤታቸውን ወንበር እንዳጡ ተነገረ፤ የሌበር ፓርቲ አናሳ ወይም አብላጫ የምክር ቤት ወንበሮችን በማሸነፍ ቀጣዩን የአውስትራሊያ መንግሥት እንደሚያቆም የABC ቴሌቪዥን የምርጫ ተንታኝ ተነበየ።

Election 2025.png

Millions turned out to vote in the 2025 federal election on Saturday, and counting is underway. Credit: AAP / Dan Himbrechts

በመላ አውስትራሊያ የፌዴራል 2025 ምርጫ ጣቢያዎች የመራጮችን ድምፅ መቀበል አቁመው ተዘግተዋል።

የድምፅ ቆጠራው ተጀምሯል።

ከ50 ፐርሰንት በታች ይፋ የሆነውን የድምፅ ቆጠራ ተከትሎ የሌበር ፓርቲ የምርጫውን ሂደት በአሸናፊት በማጠናቀቅ መልሶ ቀጣይ የፌዴራል መንግሥት እንደሚያቆምና አንቶኒ አልባኒዚም በጠቅላይ ሚኒስትርነታቸው እንደሚቀጥሉ አመላክተዋል።

ከፓርቲያቸው ድል መነሳት አልፎ የተቃዋሚ ቡድን መሪው ፒተር ዳተን የኩዊንስላንድ ዲክሰን የምክር ቤት ወንበር በሌበር ፓርቲ ዕጩ አሊ ፍራንስ ተወስዷል።


1 min read

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now