ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን ባደረበት ሕመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

ነቢይ ባደረበት ሕመም ሕክምና ሲከታተል ቆይቶ፤ ድንገት ያረፈው ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ረፋዱ ላይ ነው።

mekonnen.png

Author and Poet Nebiy Mekonnen. Credit: Supplied

የአዲስ አድማስ ዝግጅት ክፍል፣ የጋዜጣው መሥራችና ዋና አዘጋጅ የነበረው ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን ሕይወት ማለፉን ልጁ ራዕይ ነቢይ ገልጧል።

ከአዲስ አድማስ መሥራቾች አንዱ የሆነውና በዋና አዘጋጅነት ጋዜጣዋን በመምራት ተወዳጅ ካደረጓት በቀዳሚነት የሚጠቀሰው ነቢይ ብርቱ ተርጓሚ፣ ገጣሚና ወግ አዋቂ የጥበብ ሰው በመሆኑ ይታወቃል።

admas.jpg

ነቢይ በደርግ ዘመን በእስር ላይ እያለ Gone with the wind የተሰኘውን የማርጋሬት ሚቼል መፅሀፍ በሲጋራ ወረቀት ላይ ወደ አማርኛ እንደተረጎመም ይነገርለታል።

ነቢይ የፃፋቸው ግጥሞች ወደ እንግሊዝኛ እና ፈረንሳይኛ የተተረጎሙ ሲሆን፤ በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ በተከታታይ ይፅፋቸው በነበሩ "የኛ ሰው በአሜሪካ" የተሰኘው የጉዞ ማስታወሻ ተወዳጅነትን አትርፎለታል።

ነቢይ ሕይወቱ ያለፈው በተወለደ በ68 ዓመቱ ሲሆን የሶስት ሴት ልጆች አባት ነበር። የቀብሩ ሥነ ሥርዓት ባለቤቱ እና ልጁ ከውጭ ሀገር ከመጡ በኋላ እንደሚፈፀም ሸገር ኤፍኤም 102·1 አስደምጧል።


1 min read

Published

Updated

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now