የመከላከያ ሚኒስትር ሊንዳ ሬይኖልድስ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ግፊ እየበረታባቸው ነው

*** ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ክርስቲያን ፖርተር "ከኃላፊነታቸው ይገለሉ" የሚለውን ጥሪ እንደማይቀበሉ አስታወቁ።

SBS Amharic

Source: SBS Amharic

የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉን በሕግ ድጋፍ ከቆሙላት አንዲት ሴት ወሲባዊ ጥቃት ጋር አያይዘው በተጠርጣሪነት ያነሱት ጠበቃ ጉዳዩ ገና ዕልባት ያላገኘ መሆኑን ገለጡ።

ይሁንና ዐቃቤ ሕግ ክሪስቲያን ፖርተር ከቶውንም በሴቲቱ ላይ ወሲባዊ ጥቃት አልፈጸምኩም ሲሉ አስተባብለዋል። 

Attorney-General Christian Porter
Attorney-General Christian Porter. Source: AAP

ምንም እንኳ የኒው ሳውዝ ዌይልስ ፖሊስ ከወሲባዊ ጥቃት ጋር ምርመራውን የዘጋ ሲሆን፤ የደቡብ አውስትራሊያ ኮሮነር ዴቪድ ዊትል ግና የግለሰቧ አሟሟት በውል ያልተቋጨ ስለሆነ ፖሊስ ተጨማሪ ምርመራ እንዲያካሂድ ጠይቀዋል።   

 በሌላ በኩል በጅሮንድ ጆሽ ፍራይደንበርግ አቶ ፖርተር በተጠረጠሩበት ጉዳይ በሕግ ተጠያቂነታቸው እስካልሆኑ ድረስ ከወንጀል ድርጊት ነፃ የመሆናቸው ሕጋዊ መብት ሊጠበቅላቸው እንደሚገባና እንደ ሥራ ባልደረባነታቸውም ድጋፋቸውን እንደሚቸሯቸው ገልጠዋል።   

ይሁንና የግለሰቧ ጓደኛና የሕግ ባለሙያ የሆኑት ማይክል ብራድሌ ማስተባበያ ብቻውን በቂ ባለመሆኑ ይፋ የሆነ ምርመራ ሊካሄድ እንደሚገባ ተናግረዋል። 

የሌበር መሪ አንቶኒ አልባኒዚም በበኩላቸው በተመሳሳይ መልኩ በቀድሞው የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ዳይሰን ሄይደን ላይ የተካሄደው ዓይነት የወሲባዊ ጥቃት ምርመራ እንዲካሄድ አተያያቸውን ሰንዝረዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም የመከላከያ ሚኒስትር ሊንዳ ሬይኖልድስ የቀድሞ የሚዲያ አማካሪያቸውንና ቢሯቸው ውስጥ ወሲባዊ ጥቃት ደርሶብኛል ብላ አቤት ብላ ያለችውን ብሪታኒ ሂገንስን  "lying cow" ብለው በመሳደባቸው ከሚኒስትርነት ኃላፊነታቸው እንዲነሱ ጥሪዎች እየቀረቡባቸው ነው። 

ሚኒስትሯ ሂገንስን "lying cow" ማለታቸውን ያላስተባበሉ ሲሆን ያን ያሉት ግና ለሂገንስ የሰጡት ድጋፍ በሂገንስ ተዛብቶ በመቅረቡ እንደሆነ አልሸሸጉም። ሚኒስትር ሬይኖልድስ በልብ ሕመም ምክንያት በሐኪም ፈቃድ ዕረፍት ላይ ይገኛሉ። 

Defence Minister Linda Reynolds
Defence Minister Linda Reynolds has come under fire for allegedly calling Brittany Higgins a "lying cow". Source: AAP

የዋሪንጋህ የግል የምክር ቤት ተመራጯ ዛሊ ስቲጋል ከሚኒስትሯ አንደበት ወጡ የተባሉት ቃላቶች ትክክል ከሆነ የብሪታኒ ሂገንስን ብርታት የሚያኮስስ ሊሆን እንደሚችልና የወ/ሮ ሬይኖልድስ በኃላፊነታቸው መቀጠልም አስተማማኝ ሊሆን እንደማይችል አመላክተዋል። 

የታዝማኒያ የግል ተመራጭ ሴናተር ጃኪ ላምቢ በፊናቸው ሚኒስትሯ "በአስቸኳይ ከስልጣናቸው ሊነሱ ይገባል" ሲሉ ቁርጥ ያለ አተያያቸውን ሰንዝረዋል። 

የሌበር ሴናተር ፔኒ ዎንግ በበኩላቸው "ይህ ተቀባይነት የሌለው አባባል መሆኑ ግልጽ ነው" በማለት ሚኒስትር ሬይኖልድስ አደባባይ ወጥተው ማስረዳት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ሆኖም ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን የመከላከያ ሚኒስትር ሊንዳ ሬይኖልድስ ብሪታኒ ሂገንስን "lying cow" በማለታቸው "በጣሙን ተጸጽተዋል" አባባላቸውም ከድጋፍ አሰጣጡ ጋር ባላቸው የተለየ አተያይ እንጂ በቀጥታ ከወሲባዊ ጥቃቱ ጋር የተያያዘ እንዳልሆነ በማመላከት አለዝበው ገልጠዋል። 

የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ክርስቲያን ፖርተር ጉዳይንም አስመልክተው  እንደ በጅሮንድ ጆሽ ፍራይደንበርግ አቶ ፖርተር በተጠረጠሩበት ጉዳይ በሕግ ተጠያቂነታቸው እስካልሆኑ ድረስ ከወንጀል ድርጊት ነፃ የመሆናቸው ሕጋዊ መብት ሊጠበቅላቸው እንደሚገባ በመግለጽ ከጎናቸው እንደሚቆሙ ተናግረዋል።

አቶ ፖርተር ከሁለት ሳምንት የአዕምሮ ጤና ዕረፍት ሲመለሱም በሥራ ገበታቸው ላይ እንደሚሠማሩ ጠቁመዋል።   

 


2 min read

Published

Updated

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now