የግሪንስ ፓርቲ መሪ የምክር ቤት ወንበራቸውን ሊያጡ ወይም ሊያገኙ ይችላል የሚል የስጋትና ተስፋ ውዥቀት ተፈጥሯል

የግሪንስ ፓርቲ ሁለት የብሪስበን የምክር ቤት ወንበሮችን በሌበር ፓርቲ ተነጠቀ

Adam Bandt.png

Australian Greens Adam Bandt addresses the crowd at Melbourne's 2025 federal election reception. Credit: AAP / Diego Fedele

በቤቶች ጉዳዮችና ቤት አልባነት ቃል አቀባይ ማክስ ሻንድለር ማትኸር ተይዞ የነበረው የአውስትራሊያ ግሪንስ ፓርቲ የግሪፊዝ ምክር ቤት ወንበርን እንደሚያጡ የሬድብሪድጅ ቡድን ዳይሬክተር ሳይመን ዌልሽ ተናግረዋል።

በግሪንስ ፓርቲ መሪ አዳም ባንድት ተይዞ ያለው የሜልበርን ከተማ ምክር ቤት እንዲሁ በግሪንስ ፓርቲ ስር መቆየትና አለመቆየት ለጥርጣሬ መዳረጉን የአክሰንት ምርምር ዋና ኃላፊ ሾን ራትክሊፍ አመላክተዋል።

እንዲሁም በግሪንስ ፓርቲ ስቴፈን ቤትስ ተይዞ የነበረው ወደ ሌበር ማዶና ጃሬት እንደሚሸጋገር ይጠበቃል።

የግሪንስ መሪ ባንድት ቀደም ሲል የሜልበርን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የግሪንስ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ወንበሮችን ይዞ እንደሚቆይና ሁለቱን የብሪስበን የምክር ቤት ወንበሮች ፓርቲያቸው ሊያጣ እንደሚችል ተናግረው ነበር።

ይሁንና የግሪንስ ፓርቲ ዕጩ ሳማንታ ራትማን የሜልበርን ዊልስ የምክር ቤት ወንበርን ከሌበር ፒትር ካሂል ሊወስዱ እንደሚችል ተስፋ መኖሩን፤ ራትክሊፍ አመላክተዋል።

በተጨማሪም የግሪንስ ፓርቲ ኒው ሳውዝ ዌልስ ውስጥ የሪችመንድን እንዲሁም የብሪስበን ራያን የምክር ቤት ወንበሮችን የማግኘት ዕድሎች እንዳሉት ተነግሯል።


Share

1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now