የኒው ሳውዝ ዌይልስ ፕሪሚየር ግላዲስ በርጂክሊያን ቪክቶሪያ ላይ በኮሮናቫይረስ ሳቢያ ተጥሎ የነበረው የወሰን ገድብ ከኖቬምበር 23 ጀምሮ እንደሚነሳ አስታወቁ።
ቪክቶሪያ ላይ ለአንድ ወር ተጥሎ ቆይቶ የነበረው ደረጃ አራት የኮረናቫይረስ ገደቦችን አክሎ ከአራት ወራት በላይ የኒው ሳውዝ ዌይልስና ቪክቶሪያ ወሰኖች ተዘግተው ቆይተዋል።
ፕሪሚየር በርጂክሊያን ቪክቶሪያን ጨምሮ ከመላው አውስትራሊያ ወደ ኒው ሳውዝ ዌይልስ የሚመጡት ጎብኚዎች ሁሉ በመልካም ሁኔታ እንደሚያስተናገዱ ገልጠዋል።
በሌላም በኩል ቪክቶሪያ ዛሬን ጨምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት አንድም በቫይረሱ የተጠቃ ግለሰብ ወይም ያለፈ ሕይወት አልተመዘገበም።
ባለፉት14 ቀናት ቪክቶሪያ ውስጥ የቫይረሱ ተዛማችነት 1.7 ሲሆን ምንጫቸው ያልለየ 2 ተመዝግቧል።

