ቪክቶሪያውያን ከኖቬምበር 23 ጀምሮ ወደ ኒው ሳውዝ ዌይልስ መጓዝ ይችላሉ

*** ቪክቶሪያ ውስጥ ዛሬን ጨምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት በኮሮናቫይረስ የተያዙና የሞቱ ሰዎች አልተመዘገበም

NSW Premier Gladys Berejiklian

NSW Premier Gladys Berejiklian Source: AAP

የኒው ሳውዝ ዌይልስ ፕሪሚየር ግላዲስ በርጂክሊያን ቪክቶሪያ ላይ በኮሮናቫይረስ ሳቢያ ተጥሎ የነበረው የወሰን ገድብ ከኖቬምበር 23 ጀምሮ እንደሚነሳ አስታወቁ።

ቪክቶሪያ ላይ ለአንድ ወር ተጥሎ ቆይቶ የነበረው ደረጃ አራት የኮረናቫይረስ ገደቦችን አክሎ ከአራት ወራት በላይ የኒው ሳውዝ ዌይልስና ቪክቶሪያ ወሰኖች ተዘግተው ቆይተዋል።

ፕሪሚየር በርጂክሊያን ቪክቶሪያን ጨምሮ ከመላው አውስትራሊያ ወደ ኒው ሳውዝ ዌይልስ የሚመጡት ጎብኚዎች ሁሉ በመልካም ሁኔታ እንደሚያስተናገዱ ገልጠዋል። 

 በሌላም በኩል ቪክቶሪያ ዛሬን ጨምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት አንድም በቫይረሱ የተጠቃ ግለሰብ ወይም ያለፈ ሕይወት አልተመዘገበም።

ባለፉት14 ቀናት ቪክቶሪያ ውስጥ የቫይረሱ ተዛማችነት 1.7 ሲሆን ምንጫቸው ያልለየ 2 ተመዝግቧል።   

 

 

 


1 min read

Published

Updated

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now