ድሬዳዋ ቀፊራ አካባቢ የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው ምርቶች እንዲወገዱ ከተደረጉበት ጉድጓድ ቆፍረው በማውጣት ሊሸጡ የነበሩ 17 ግለሰቦች በፖሊስ በቁጥጥር ስር ዋሉ

ከተለያዩ ሱቆች ተሰብስበው ተቀብረው የነበሩት የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው ምርቶች 1ሺ700 ሊትር የምግብ ዘይት፣ ዱቄት ወተት እና ሩዝ እንደነበሩ ተገልጧል።

Expired goods.png

Credit: Supplied

የመጠቀሚያ ግዜ ያለፈባቸው ምርቶች እንዲወገዱ ከተደረጉበት ጉድጓድድ ቆፍረው በማውጣት ለመሸጥ በመዘጋጀት ላይ የነበሩ 17 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ድሬ ፖሊስ ገለፀ።

በከተማዋ ቀፊራ እየተባለ በሚጠራው የገበያ ስፍራ በጤና ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉና የአገልግሎት ግዜ ያለፈባቸው ምርቶች ከተለያዩ ሸቀጣሸቀጥ ሱቆች 1ሺ700 ሊትር የምግብ ዘይት፣ ዱቄት ወተት እና ሩዝ ተለይቶ በመሰብሰብ በጉድጓድ ተቆፍሮ እንዲወገድ መደረጉን የገለፀው ፖሊስ ተከሳሾቹ ምርቱ ከተቀበረበት ጉድጓድ ቆፍረው በማውጣት ለመሸጥ በመዘጋጀት ላይ እንዳሉ በህብረተሰቡ ጥቆማ መሰረት መያዛቸውን አስታውቋል።

የአዲስ ከተማ ፖሊስ ጣቢያና የመጋላ ፖሊስ ጣቢያ በጋራ በሰሩት ቅንጅታዊ ስራ ከጉዳዩ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸው 10 ሴት እና 7 ወንድተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ ገልጧል።


1 min read

Published

Updated

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now