የዓለም ምርጥ የእግር ኳስ ተጫዋቹ አጀንቲናዊው ዲያጎ ማራዶና ለብሶት የነበረው የብሔራዊ ቡድን ጀርሲ በ $12.5 ሚሊየን ዶላር ተሸጠ

*** ሳዑዲ አረቢያ ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ ወደ አገሪቱ የተለያዩ ግዛቶች የዘለቀ 45.6 ቶን ጫት መያዟንና 11 ኢትዮጵያውያንን ለእሥር መዳረጓን ገለጠች።

News

A football shirt worn by Argentina's Diego Maradona during the 1986 World Cup quarter-final match against England. Source: Getty

በዓለም ዝነኛ የነበረው የእግር ኳስ ተጫዋች አጀንቲናዊው ዲያጎ ማራዶና ለብሶት የነበረው የብሔራዊ ቡድን ጀርሲ በጨረታ $12.5 ሚሊየን የአውስትራሊያ ዶላር ተሸጠ።

ማራዶና ኖቬምበር 2020 ከዚህ ዓለም በ60 ዓመቱ በሞት የተለየ ሲሆን፤ ለአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን 10 ቁጥር ለብሶ በ1986 የዓለም ዋንጫ የሩብ ፍፃሜ ከእንግሊዝና ሜክሲኮ ጋር ተጫውቷል። 

በእኒዚያ ግጥሚያዎች ወቅትም በዓለም የእግር ኳስ ታሪክ ዝነኛ የሆኑ ሁለት ግቦችን አስቆጥሯል። 

አንደኛዋን ግብ ያስገባው በአርጀንቲናና እንግሊዝ መካከል በተደረገው ግጥሚያ የሁለተኛው ግማሽ ጨዋታ ሊፈፀም ስድስት ደቂቃዎች ሲቀሩ በእጁ ነክቶ ያስገባት ግብና እስካሁንም ድረስ "የእግዚአብሔር እጅ" በሚል የምትታወሳዋና አወዛጋቢዋ ግብ ናት።

News
1986 Football World Cup, Argentina's Diego Maradona scores 1st goal with his Hand of God, past England goalkeeper Peter Shilton. Source: Getty

ማራዶና ምንም እንኳ በእጁ ነክቶ ግቧን ቢያስቆጥርም በወቅቱ ዳኛው ልብ ብሎ ስላልተመለከተና እንደ ዛሬው የቪዲዮረዳት ዳኛ ቴክኖሎጂ ባለመኖሩ በግብነት ፀድቃ አርጀንቲና እንግሊዝን 1 ለ 0 መምራት ችላለች። 

ቀጥሎም ከአራት ደቂቃዎች በኋላ ሌላ "የክፍለ ዘመኑ ግብ" የተሰኘት ግብ በማስቆጠሩ አርጀንቲና እንግሊዝን 2 ለ 1 እንድትረታ አብቅቷል። 

News
Argentinian forward Diego Armando Maradona (3rd L) scoring his second goal, or goal of the century, on June 22, 1986 in Mexico City. Source: Getty

ጫት ሳዑዲ አረቢያ

የሳዑዲ ባለስልጣናት በትናንትናው ዕለት ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ ወደ አገሪቱ የተለያዩ ግዛቶች የዘለቀ 45.6 ቶን ጫትና 760 ኪሎ ግራም ሃሺሽ በድንበር የፀጥታ ኃይላት ቁጥጥር ስር ማዋላቸውን አስታወቁ።

የድንበር ፀጥታ ኃይላቱ ከጫትና የአደንዛዥ ዕፆቹ ጋር ተያይዞ 41 የሳዑዲ ዜጎችን፣ 11 ኢትዮጵያውያን፣ ሰባት የመናውያንና ሁለት የፓኪስታን ዜጎች ለእሥር መዳረጋቸውን የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ገልጧል። 

ቀደም ሲልም ኤፕሪል 8 ወደ ሳዑዲ ዘልቆ የገባ 39 ቶን ጫት መያዙም ተጠቅሷል። 

 

 

 


2 min read

Published

Updated

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now