አንድ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ኮሚቴ "በብዥታና ቸልተኝነት" ሳቢያ ከ2.1 ሚሊየን በላይ አውስትራሊያውያን የኮቪድ-19 ሶስተኛ ዙር ክትባት ያለመከተባቸውን ሪፖርት አደመጠ።
የፌዴራል ክትባት ስርጭት ዋና ኃላፊ ሌተና ጄኔራል ፍሬዌን ኮሚቴው ፊት ቀርበው 11 ፐርሰንት ያህል ለተጨማሪ ክትባት መመዘኛ ብቁ የሆኑ ግለሰቦች የሶስተኛ ዙር ክትባታቸውን አለመከተባቸውን ተናግረዋል።
ጄኔራሉ የሶስተኛውን ዙር ክትባት ካልተከተቡት ውስጥ ከፍተኛውን ቁጥር የያዙት ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በታች የሆኑ ግለሰቦች መሆናቸውንም አክለው ገልጠዋል።
ታዝማኒያ ፕሪሚየር
የታዝማኒያ ምክትል ፕሪሚየር ጀርሚ ሮክሊፍ በዚህ ሳምንት መጨረሻ የታዝማኒያ ፕሪሚየር ሆነው ቃለ መሃላ እንደሚፈጽሙ ይጠበቃል።
በዚህ ሳምንት መጅመሪያ ሰኞ ዕለት ፕሪሚየር ፒተር ጋትዊን በፍቃዳቸው ከታዝማኒያ ፕሪሚየርነትና የባስ ምክር ቤት አባልነታቸውን በፈቃዳቸው ለቅቀዋል።

በፕሪሚየር ጋትዊን እግር ለመተካት እስካሁን ፈቃደኝነታቸውን የገለጡት ከ2014 ጀምሮ እስካሁን ድረስ በምክትል ፕሪሚየርነት ያገለገሉት አቶ ሮክሊፍ ብቻ ናቸው።
በእሳቸው ምትክ ምክትል ፕሪሚየር ለመሆን የትራንስፖርት ሚኒስትር ማይክል ፈርጉሰንና ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ኢሊስ አርቸር እንደሚፎካከሩ ተነግሯል።

