ለሳፋሪኮም የሞባይል ገንዘብ ዝውውር ተፈቀደ

የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ የኢትዮጵያ መንግሥት ለሳፋሪኮም የሞባይል ገንዘብ ዝውውር እንዲያደርግ በመፍቀዱ የተሰማቸውን ደስታ ገልጠዋል

Kenyan President William Ruto .jpg

Kenyan President William Ruto. Credit: W.Ruto

የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በሀገር አቀፍ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በወዳጅነት አደባባይ ተካሂዷል፡፡

በመድረኩ ላይ ለኩባንያው በሞባይል የገንዘብ ዝውውር እንዲያከናውን እንደተፈቀደ ይፋ ሆኗል።

ይህን ተከትሎም ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፥ “የኬንያ ሕዝብ ወደ ኢትዮጵያ ስመጣ ይህን እንዳስፈጽም የቤት ሥራ ሰጥቶኝ ነበር፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ይህን አገልግሎት በመፍቀዱ አመሰግናለሁ” ብለዋል።

የቴክኖሎጂ አብዮት እንደምን ተልምዷዊ ተግዳሮቶችን በመሻገር ዘላቂ ብልፅግናን ማበረከት እንደቻለና ከሳፋሪኮም ስኬት ጋርም እንደምን ተያያዥ እንደሆነ አንስተዋል።

ሳፋሪኮም በኬንያ በኤም ፔሳ የገንዘብ አገልግሎት ያገኘውን ስኬት በኢትዮጵያ ለመድገም እንደሚሠራም አስታውቋል።

ኢትዮ ቴሌኮም ከዚህ ቀደም የቴሌ ብር አገልግሎት በማስጀመር ሚሊዮኖችን ተጠቃሚ ማድረጉ ይታወሳል።


1 min read

Published

Updated

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now