ለሳፋሪኮም የሞባይል ገንዘብ ዝውውር ተፈቀደ

የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ የኢትዮጵያ መንግሥት ለሳፋሪኮም የሞባይል ገንዘብ ዝውውር እንዲያደርግ በመፍቀዱ የተሰማቸውን ደስታ ገልጠዋል

Kenyan President William Ruto .jpg

Kenyan President William Ruto. Credit: W.Ruto

የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በሀገር አቀፍ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በወዳጅነት አደባባይ ተካሂዷል፡፡

በመድረኩ ላይ ለኩባንያው በሞባይል የገንዘብ ዝውውር እንዲያከናውን እንደተፈቀደ ይፋ ሆኗል።

ይህን ተከትሎም ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፥ “የኬንያ ሕዝብ ወደ ኢትዮጵያ ስመጣ ይህን እንዳስፈጽም የቤት ሥራ ሰጥቶኝ ነበር፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ይህን አገልግሎት በመፍቀዱ አመሰግናለሁ” ብለዋል።

የቴክኖሎጂ አብዮት እንደምን ተልምዷዊ ተግዳሮቶችን በመሻገር ዘላቂ ብልፅግናን ማበረከት እንደቻለና ከሳፋሪኮም ስኬት ጋርም እንደምን ተያያዥ እንደሆነ አንስተዋል።

ሳፋሪኮም በኬንያ በኤም ፔሳ የገንዘብ አገልግሎት ያገኘውን ስኬት በኢትዮጵያ ለመድገም እንደሚሠራም አስታውቋል።

ኢትዮ ቴሌኮም ከዚህ ቀደም የቴሌ ብር አገልግሎት በማስጀመር ሚሊዮኖችን ተጠቃሚ ማድረጉ ይታወሳል።

Share

Published

Updated

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service