ሩስያን ከተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ለማገድ በቀረበው የአቋም መግለጫ ላይ ከ193 የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ አባላት ሁለት ሶስተኛ የይሁንታ ድምፅ አግኝቶ አልፏል።
ትናንት ኤፕሪል 7, 2022 በተካሔደው የጠቅላላ ጉባኤ ድምፅ አሰጣጥ ላይ 93 አገራት ይሁንታቸውን ሲቸሩ 24 ተቃውመዋል፤ 58 ድምፀ ተአቅቦ አድርገዋል።

ድጋፋቸውን ካሰሙት ውስጥ ዩናይትድ ስቴትስ፣ አውስትራሊያና ሶስት የአፍሪካ አገራት ሲገኙበት፤ ተቃውሞ ካሰሙት ውስጥ ሩስያ፣ ቻይናና ኢትዮጵያን ጨምሮ ዘጠኝ የአፍሪካ አገራት ይገኙበታል።
ለእገዳው ዋነኛ ምክንያት ተደርጎ የተወሰደው የሩስያ ጦር ዩክሬይን ውስጥ ፈጽሟቸዋል ከተባሉት የሰላማዊ ሰዎች ግድያዎች ጋር ተያይዞ ነው።
በሌላ በኩል በተመድ የሩስያ ምክትል ቋሚ ተወካይ ኩዝሚን ሩስያ ዕለቱኑ ምክር ቤቱን ለቅቃ ለመሰናበት መወሰኗን አስታውቀዋል።
አክለውም፤ ምክር ቤቱ በአንድ የመንግሥታት ቡድን የአጭር ጊዜ ዓላማ በበላይነት የተያዘ እንደሆነ ተናግረዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር
የዩናይትድ ስቴትስ ዕጩ አምባሳደር ዕጩነታቸው ከፀደቀ የአውስትራሊያንና ዩናይትድ ስቴትስን ወዳጅነት ይበልጡን ለማጠናከር ታትረው እንደሚሠሩ አስታወቁ።
የቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ ሴት ልጅ ካሮላይን ኬኔዲ በአውስትራሊያ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ሆነው ወድ ካንብራ ለመምጣት ዕጩነታቸው ይሁንታ ለማግኘት በሂደት ላይ ይገኛል።

ካሮላይን ኬኔዲ ቀደም ሲል በፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ አስተዳደር በጃፓን የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዘደንት ሆነው አገልግለዋል።
ታዝማኒያ ፕሪሚየር
ጀርሚ ሮክሊፍ በሊብራል ፓርቲ ስብሰባ ያለተቀናቃኝ 47ኛው አዲሱ የታዝማኒያ ፕሪሚየር ሆነው በሙሉ ድምፅ ተመረጡ።

አቶ ሮክሊፍ በፕሪሚየርነት ለመመረጥ የበቁት ሰኞ ዕለት ከታዝማኒያ ፕሪሚየርና ባስ የምክር ቤት አባልነታቸው በፈቃዳቸው በለቀቁት ፒተር ጋትዊን ምትክ ነው።

