የአውስትራሊያ ፌዴራል መንግሥት የኮሮናቫይረስን ለመፋለም ያግዝ ዘንድ ተጨማሪ 300,000 ክትባቶችን ለኒው ሳውዝ ዌይልስ እንደሚልክ አስታወቀ።
ተጨማሪ የሚላኩት የኮሮናቫይረስ ክትባት ዓይነቶች አስትራዜኒካና ፋይዘር ሲሆኑ፤ በቀዳሚነት የሚሰጡትም ለሲኒ የደቡብ ምዕራብ ነዋሪዎች ነው።
ኒው ሳውዝ ዌይልስ ዛሬ ዕለተ ሐሙስ 38 ነዋሪዎቿ በቫይረሱ መጠቃታቸውን አስታውቃለች። ከ38ቱ ውስጥ 18ቱ ራሳቸው አግለልለው የሚገኙ የማኅበረሰብ አባላት እንደሆኑም ተገልጧል።
ቀደም ሲል ለሁለት ሳምንታት ተጥሎ የነበረው ገደብ ለሶስተኛ ሳምንት መራዘምን ተክትሎ የፌዴራል መንግሥቱ ጊዜያዊ ድጎማ እንደሚያደርግ ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን አስታውቀዋል።

ምንም እንኳ ከ $325 - $500 ጊዜያዊ አስቸኳይ ድጎማውን ለመቀበል የሚችሉት ከ$10,000 በታች ተቀማጭ ያላቸው ቢሆንም ከሶስተኛው ሳምንት ጀምሮ ባሉት ታካይ ቀናት የ$10 ሺህ ተቀማጭ ጣራ እንደሚነሳ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጠዋል።

