የብሔራዊ ፀረ - ሙስና ኮሚሽን ግብረ ኃይል በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዲፓርትመንት እየተቋቋመ ነው

*** የዓለም ባንክ ለዩክሬይን የመንግሥትና ማኅበራዊ ሠራተኞች ደመወዝ ክፍያ የሚውል $1.5 ቢሊየን ሰጠ

News

Attorney-General Mark Dreyfus. Source: Getty

አዲሱ የአልባኒዚ መንግሥት የብሔራዊ ፀረ - ሙስና ኮሚሽን ድንጋጌ በዚህ ዓመት መጨረሻ ፀድቆ በ2023 አጋማሽ ላይ ሥራውን እንደሚጀምር ይጠበቃል።  

አዲሱ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ማርክ ድሬይፈዝ የሌበር ፓርቲ በአገር አቀፍ ምርጫ ዘመቻ ወቅት የገባውን ሁነኛ ቃል ዕውን ለማድረግ በዲፓርትመንታቸው ውስጥ ግብረ ኃይል እንዲቋቋም አድርገዋል። 

ሌበር የኮሚሽኑንን ተግባራትና ስልጣን አስመልክቶ ከግል ተመራጭ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ጋር ይመክራል፤ እንዲሁም ከክፍለ አገራት ፀረ - ሙስና ኮሚሽኖች የአፈፃፃም መርሃ ግብር የሚወስዳቸውንም ይመለከታል። 

አቶ ድሬይፈዝ ግብር ላይ ሊያውሉት አስበውት ስላለው ኮሚሽን ለ A-B-C ሲናገሩ፤ 

"ኮሚሽኑ ነፃና ገለልተኛ ይሆናል። ብርቱ ስልጣን ያለው ይሆናል። የሮያል ኮሚሽን ስልጣኖች ይኖሩታል። ብርቱና መዋቅራዊ ሙስናን ይመረምራል። ከተለያዩ ምንጮች ጥቆማዎችን ይቀበላል፤ ምስጢራዊነታቸው የተጠበቀ ይሆናል። በይፋ የሙስና ምርመራ ስሚዎችን ያካሂዳል። እነዚህ ሁሉ በጣሙን አስፈላጊ ናቸው፤ ካለፈው መንግሥት ረቂቅ ድንጋጌም የተለየ ነው" ብለዋል። 

ዩክሬይን - የዓለም ባንክ 

የዓለም ባንክ ተጨማሪ $1.5 ቢሊየን ለዩክሬይን ሰጠ።

ድጎማው ለመንግሥትና ማኅበራዊ ሠራተኞች ደመወዝ ክፍያ የሚውል ይሆናል።

ባንኩ እስካሁን ለዩክሬይን ከ $4 ቢሊየን በላይ ድጎማ አድረጓል።

የልማት አበዳሪው ባንክ ከተለያዩ አገራት ለጋሾች ጋር በመተባበር የደቀቀውን የዩክሬይን ምጣኔ ሃብት ለመታደግ፣ የጤና፣ የትምህርትና ማኅበራዊ ደኅንነት ለኡክሬናውያን ተደራሽነት እንዲሆኑ እየሠራ መሆኑን ገልጧል። 

 

 


1 min read

Published

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now