ተዋናይ ዊል ስሚዝ በ94ኛው የኦስካር ሽልማት ሥነ ሥርዓት ወቅት የመድረክ አጋፋሪ የነበረውን ክሪስ ሮክ በጥፊ መማታቱን ተከትሎ ለሚቀጥሉት 10 ዓመታት በኦስካር የሽልማት ሥነ ሥርዓቶች ላይ እንዳይገኝ ታገደ።
እንዲሁም ለሚቀጥለው አንድ አሠርት ዓመት የተንቀሳቃሽ ምስል ሥነ ጥበብና ሳይንስ አክዳሚ ኩነቶች ላይ እንዳይገኝም ገደብ ተጥሎበታል።
ይሁንና ቦርዱ ዊልል ስሚዝ ባለፈው ወር በ King Richard ትወናው ያገኘውን ምርጥ ተዋናይ የኦስካር ሽልማት እንዲነጠቅና ከወደፊት የኦስካር ሽልማት ዕጩነት ወይም አሸናፊነት እንዲታገድ ግና አልወሰነም።
አገር አቀፍ ምርጫ
የተቃዋሚ ቡድን መሪ አንቶኒ አልባኒዚ ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን የፌዴራል ምርጫ ቀንን እስካሁን ባለመቁረጣቸው ትችት ሰነዘሩ።
የአገር አቀፍ ምርጫውን ለሜይ 14 ወይም ለሜይ 21 ለመጥራት ሁለት ቅዳሜዎች ብቻ ቀርተዋል።
በነገው ዕለት እሑድ የምርጫ ቀን ቆረጣ ካልተደረገ የምክር ቤት አባላት በሚቀጥለው ሳምንት ወደ ካንብራ ለመመለስ ግድ ይሰኛሉ።
አቶ አልባኒዚ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምርጫ ጥሪውን የማዘግየቱን ሁነት ልክ የጨዋታ ያህል እየቆጠሩት ነው፤ ምርጫው ሲጠራም ጠረጴዛ ላይ የሚያኖሯቸው ፖሊሲዎች እንደሌላቸውም ተናግረዋል።
ዊል ስሚዝ

