ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ከዓለም 18ኛ ደረጃን ያዘች

በቦምብ ፍንዳታ ፈርሶ የነበረውና ሩስያን ከክራሚያ ጋር የሚያገናኘው ብቸኛው ድልድይ በከፊል ግልጋሎት ላይ መዋል ጀመረ

Farmers threshes wheat to loosen the edible grain from the chaff.jpg

Farmers threshes wheat to loosen the edible grain from the chaff in the outskirts of Gondar, Ethiopia. Credit: EDUARDO SOTERAS/AFP via Getty Images

የዩናይትድ ስቴትስ ግብርና ሚኒስቴር በወርኅ ሴፕቴምበር ባወጣው የ2022/23 የዓለም ስንዴ ምርት ውጤት ዝርዝር ኢትዮጵያ 5,700,000 ሜርትሪክ ቶን በማምረት ከዓለም 18ኛ ደረጃ ላይ መገኘቷን አመልክቷል።

በተያያዥነትም ቻይና 138,000,00 ሜትሪክ ቶን ስንዴን በማምረት ከዓለም የመጀመሪያውን ደረጃን የያዘች ሲሆን፤ ሩስያ 91,000,000 በማምረት አራተኛ፣ ዩናይትድ ስቴትስ 48,523,000 በማምረት አምስተኛ፣ አውስትራሊያ 33,000,000 በማምረት ሰባተኛ፣ ዩክሬይን 20,000,000 በማምረት ዘጠነኛ፣ ግብፅ 9,800,000 ሜትሪክ ቶን በማምረት 15ኛ ደረጃ ላይ ተመዝግበዋል።

ባለፈው የፈረንጆቹ ሴፕቴምበር ወር ምንም እንኳ የ2022/2023 የዓለም የስንዴ ምርት መጠን 78.392 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን ይሆናል ተብሎ ቢገመትም፤ ከግምቱ በላይ የ4.32 ቶን ምርት ጭማሪ አሳይቷል።

ቀጣዩ የዓለም የስንዴ ምርት ውጤት ኦክቶበር 12 ቀን 2022 / ጥቅምት 2 ቀን 2015 ይፋ ይሆናል።

ክራሚያ

የፍንዳታ አደጋ ደርሶበት የነበረውና ሩስያን ከክራሚያ ጋር የሚያገናኘው ብቸኛው ከርች ድልድይ በከፊል ግልጋሎት ላይ መዋል ጀመረ።

ለሩሲያ የጦር መሳሪያዎችን ወደ ዩክሬይን ግንባር ለማመላለስ ጥቅም ላይ ይውል የነበረው ድልድይ የፍንዳታ አደጋ በገጠመው ወቅት አንድ ከባድ የጭነት መኪና መጋየቱንና የሶስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ሩስያ አስታውቃለች።

Explosion causes fire at the Kerch bridge in the Kerch Strait, Crimea.jpg
Explosion causes fire at the Kerch bridge in the Kerch Strait, Crimea on October 08, 2022. Credit: Vera Katkova/Anadolu Agency via Getty Images
የሩስያ የምርመራ ኮሚቴ ተወካይ ስቪትላና ፐትሬንኮ ባለስልጣናት በአደጋው ሕይወታቸው ያለፈውን ሶስት ግለሰቦች ማንነት ለማጣራት ምርመራ እያካሔዱ መሆኑን ገልጠዋል።

የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን

ኢትዮጵያን አስመልክቶ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን እንዲመረምር በተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ለተሰየመው በኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተጠባቢዎች ኮሚሽን ለአንድ ዓመት በውክልናው እንዲቀጥል ይሁንታን አግኝቷል።

ውሳኔው በ21 ድጋፍ፣ 19 ተቃውሞና 7 ድምፀ ተዐቅቦ አልፏል።


ምክር ቤቱ ሰሜን ኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሔደ ባለው ግጭት በሁለቱም ተፋላሚ ወገኖች ዘንድ ማናቸውም ዓይነት የሰብዓዊ መብቶች አመፆችና ጥሰቶች፣ የዓለም አቀፍ ሕግን የመተላለፍ ድርጊቶች በአስቸኳይ እንዲገቱ ዳግም ጥሪ አቅርቧል።

ውክልናው ለአንድ ዓመት የተራዘመለት የሰብዓዊ መብቶች ቡድን በአምሳ - ሁለተኛው ስብሰባ የቃል ሪፖርት እንዲያስደምጥ፣ በአምሳ - አራተኛው ስብሰባ የፅሁፍ ሪፖርት እንዲያቀርብ፣ በሰባ - ስምንተኛው ስብሰባ ጠቅላላ ጉባኤው እንዲመክርበት መመሪያ ሰጥቷል።

Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service