አውስትራሊያ በሯን ከፈረንጆች ገና በዓል በፊት ለዓለም አቀፍ በረራ ለመክፈት እየተዘጋጀች ባለችበት ወቅት የኳንታንስ አየር መንገድ ዋና ሥራ አሥፈፃሚ አላን ጆንስ ለሁሉም የባህር ማዶ መንገደኞች የኮቪድ-19 ክትባት ያልተክተቡ መንገደኞችን ላለማሳፈር ዕቅድ መያዙን አስታውቀዋል።
አየር መንገዱ የዓለም አቀፍ በረራውን ከተወሰኑ አውሮፕላን ማረፊያዎች ከዲሴምበር አጋማሽ ጀምሮ ይጀምራል። ኳንታስ ለበረራ ቅድሚያ ከሰጣቸው አገራት ውስጥ ጃፓን፣ ሲንጋፖር፣ ዩናይትድ ስቴትስና እንግሊዝ ይገኙበታል።
አቶ ጆይስ የአውሮፕላን አስተናጋጆች፣ ፓይለቶችና የአውሮፕላን ማረፊያ ሠራተኞች እስከ ኖቬምበር 15 የተቀሩት ሠራተኞች በማርች 2022 መጨረሻ ሙሉ ክትባት ለማድረግ ግድ እንደሚሰኙ ተናግረዋል።
ዋና ሥራ አሥፈፃሚው አየር መንገዱ በቅርቡ በረራ ከመጀመሩ በፊት ፖሊሲውን ይፋ እንደሚያደርግ ሲናገሩ "ኳንታስ ክትባት የተከተቡ ሰዎችን ብቻ እንደሚጭን ግድ የሚል ዓለም አቀፍ ፖሊሲ ይኖረዋል" ብለዋል።
ይሁን'ጂ የአገር ውስጥ በረራን አስመልክቶ ገና ከውሳኔ ላይ ያልደርሱ መሆኑን ጠቁመው ኦገስት አካባቢ የአየር መንገዱን የአገር ውስጥ የክትባትና በረራ ፖሊስ ይፋ እንደሚያደርጉ ገልጠዋል።

