የእንግሊዟ ንግሥት ኤልሳቤጥ በ96 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፤ በዙፋናቸው ንጉሥ ቻርልስ ተተኩ

የዳግማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥን በስኮትላንድ መኖሪያቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየት ያስታወቀው ባኪንግሃም ቤተመንግሥት ነው። የንግሥቲቱን ሕልፈት ተከትሎም የበኩር ልጃቸው ቻርልስ በአልጋ ወራሽነታቸው አውስትራሊያን ጨምሮ የ14 አገራትና የእንግሊዝ ንጉሥ ሆነዋል።

Queen Elizabeth II.jpg

Queen Elizabeth II has died at age 96. Credit: Max Mumby/Indigo/Getty Images

የንግሥቲቱ ማረፍ በይፋ በባኪንግሃም ቤተመንግሥት በኩል የተነገረው በአውስትራሊያ ሰዓት አቆጣጠር ዓርብ ማለዳ ላይ ነው።

የቤተመንግሥቱ መግለጫ "ንግሥቲቷ ዛሬ ከቀትር በኋላ ባልሞራል በሰላም አርፈዋል" ሲል ያስታወቀ ሲሆን፤ የቅርብ ቤተሰብ አባላቱም በነገው ዕለት ከባልሞራል ወደ ለንደን እንደሚመለሱ አመልክቷል።

የንግሥቲቱን ዕረፍት ተከትለው በዙፋናቸው በንጉሥነት የተተኩት የ73 ዓመቱ ቻርልስ የእናታቸውን ከዚህ ዓለም በሞት መለየት አስመልክተው በበኩላቸው ባወጡት መግለጫ የሐዘን ስሜታቸውንና ሁነቱን "ታላቅ የኃዘን ወቅት" ሲሉ ገልጠዋል።

መጠሪያቸውም ንጉሥ ቻርልስ ሳልሳዊ ይሆናል።

የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚን ጨምሮ የበርካታ አገራት መሪዎች የሐዘን መግለጫ አውጥተዋል።


1 min read

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now