አቶ አልባኒዚ ለተሻለ የአውስትራሊያ መፃኢ ዕድል ዕውን መሆን እንደሚታትሩና አውስትራሊያውያንንም ከአክብሮት ጋር እንደሚያገለገሉ ገለጡ

***አቶ ሞሪሰን ምርጫው አውስትራሊያውያን ባለፉት አዋኪ ሶስት ዓመታት ከተፈተነ መንግሥትና ፈተና ካልገጠመው የተቃዋሚ ቡድን የሚመርጡበት መሆኑን አመላከቱ።

Prime Minister Scott Morrison (R) and Opposition leader Anthony Albanese will face off in the federal election on 21 May.

Prime Minister Scott Morrison (R) and Opposition leader Anthony Albanese will face off in the federal election on 21 May. Source: SBS

የጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን አገር አቀፍ ምርጫን ለሜይ 21 መጥራት ተከትሎ የተቃዋሚ ቡድን መሪ አንቶኒ አልባኒዚ ለአውስትራሊያና አውስትራሊያውያን ያላቸውን ርዕይ ዛሬ ከቀትር በኋላ አመላክተዋል።

አቶ አልባኒዚ አውስትራሊያውያንን ዳግም ወደ አንድነት እንደሚያመጡና የተሻለ መፃኢ ዕድል እንደሚፈጥሩ አስገንዝበዋል። 

ያለ አባት በእናት ብቻ የመንግሥት ቤት ውስጥ በችግር ያደጉ በመሆናቸው ለአውስትራሊያውያን የተሻለ ሕይወት ለመፍጠር እንደሚታትሩ ተናግረዋል።  

አያይዘውም፤ የሌበር ፓርቲ የኑሮ ውድነትን የሚያቀልሉ ዕቅዶች እንዳሉት፣ በአነስተኛ አቅም የሚሠሩ ቤቶችን እንደሚገነባ፣ የአረጋውያን ክብካቤ ቀውስንና የብሔራዊ ብሮድባንድ አውታረ መረብ እክሎችን እንደሚከላ አመላክተዋል። 

አውስትራሊያውያን በሜይ 21ዱ ምርጫ ለጠቅላይ ሚኒስትርነት ካበቋቸውም በአክብሮት እንደሚያገለግሉ፣ እምነት አጥቶ ያለውን የፖለቲካ ሥር ዓት እንደሚያቃኑና ብርቱ የፀረ መስና ኮሚሽን እንደሚያቆሙ ተናግረዋል። 

ከአቶ አልባኒዚ ቀደም ሲልም የአገራዊ ምርጫውን ቀን ለሜይ 21 የቆረጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን በጠሩት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ አውስትራሊያውያን ፖለቲካ የሰለቻቸው እንደሆነና ይልቁንም በዚህ ምርጫ መፃኢው ጊዜ በጣሙን ጠቃሚ እንደሆነ አሳስበዋል።   

አቶ ሞሪሰን ምርጫው አውስትራሊያውያን ባለፉት አዋኪ ሶስት ዓመታት ከተፈተነ መንግሥትና ፈተና ካልገጠመው የተቃዋሚ ቡድን የሚመርጡበት መሆኑን አመላክተዋል።  

 

 

 

 


1 min read

Published

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now