ሙሉቀን መለሰ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

ሙለቀን መለሰ ሕይወቱ ያለፈው በሚኖርበት ሀገረ አሜሪካ ነው

Muluken Melese.png

Muluken Melese. Credit: Supplied

ከሶስት አስርት ዓመታት ባለይ በሀገረ አሜሪካ ኑሮውን ያደረገው ሙሉቀን መለሰ የሙዚቃውን ዓለም በመተው በመንፈሳዊ የሙዝሙር ስራዎች ውስጥ ያሳልፍ እንደነበር ይታወሳል።

ሙሉቀን መለሰ በጎጃም ክፍለ ሀገር አነደድ ወረዳ ውስጥ ዳማ ኪዳነ ምሕረት በምትባል መንደር በ1946 ዓ.ም እንደተወለደ ግለታሪኩ ያወሳል።

አሥር ዓመት ሲሆነው እናቱ ስለሞቱ፤ አዲስ አበባ ይኖሩ ከነበሩ አጐቱ ጋር እንዲማር ብለው ያመጡት ሙሉቀን መለሰ ኮልፌ ሰፈር ጳውሎስ ትምህርት ቤት ሊገባ ችሏል።

ለሙዚቃ ልዩ ፍቅር የነበረው ድምፃዊው እርሱ በነበረበት አከባቢ በተከፈተው የሙዚቃ ትምህርት ቤት ገብቶ በአቶ ተፈራ አቡነ ወልድ አማካይነት ለስድስት ወራት የዘለቀ የትምህርት እገዛ አግኝቷል።

ገና የ13 ዕድሜ ታዳጊ ሳለ ሙዚቃን የጀመረው ድምፃዊው በ1958ዓ.ም በፈጣን ኦርኬስትራ ውስጥ ተቀላቅሎ በመግባት ለሁለት ዓመታት ያህል መስራት ችሏል።


Share

Published

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
ሙሉቀን መለሰ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ | SBS Amharic