የንጉሥ ቻርልስ ሳልሳዊ ንግሥና ዕወጃ ሥነ ሥርዓት በለንደን ተካሔደ

የንግሥና ሥነ ሥርዓቱ ተመሳሳይነት ባለው መልኩ ነገ አውስትራሊያ ውስጥ ይካሔዳል።

King Charles III London.jpg

(From left to right) Britain's Prince William, Camilla, the Queen Consort, King Charles III and Lord President of the Council Penny Mordaunt and Privy Council members are in the Throne Room during the Accession Council at St James's Palace, London. Credit: AAP / Jonathan Brady

በእናታቸውን ዳግማዊት ኤልሳቤጥ ሕልፈተ ሕይወት ሳቢያ አልጋ ወራሽ የሆኑት የንጉሥ ቻርልስ ሳልሳዊ የንግሥና ሥነ ሥርዓት በይፋ ለንደን ውስጥ ተካሂዷል።

ንጉሥ ቻርልስ ርዕሰ ብሔር በሆኑባት አውስትራሊያ ውስጥም የሚካሔድ ይሆናል።

ለንደን በተካሔደበት ወቅትም ከ200 በላይ እድምተኞች ንጉሥ ቻርልስ በተገኙበት አዳራሽ በእማኝነትና ተጋባዥነት ተገኝተዋል።

የንግሥት ኤልሳቤጥ አስከሬን አሁን ባለበት ባልሞራል ተነስቶ ነገ እሑድ ወደ ኢደንብራ ሆሊሩድሃውስ ቤተመንግሥት ያመራል።

ከዚያም ለመንግሥታዊ የቀብር ሥነ ሥርዓት ክንውን ማክሰኞ ዕለት ወደ ለንደን ያቀናል።

Share

Published

Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service