62 ተሳፋሪዎችን ጭኖ የተከሰከሰው የኢንዶኔዥያ ቦይንግ 737 አውሮፕላን መንገደኞች አስከሬኖችና የአውሮፕላኑ ቁርጥራጭ አካላት ተገኙ

*** ከ62ቱ ተሳፋሪዎች መካከል 10ሩ ሕጻናት ናቸው።

Amharic News 10 January 2021

Rescuers inspect debris found in the waters around the location where the Sriwijaya Air jet lost contact with air traffic controllers. Source: AP

62 ተሳፋሪዎችን ጭኖ ከጃካርታ እምብዛም ሳይርቅ የተከሰከሰው የኢንዶኔዥያ ቦይንግ 737 መንገደኞች አስከሬኖችና የአውሮፕላኑ ቁርጥራጭ የብረት አካላት ዛሬ እሑድ ከቀትር በኋላ ተገኝቷል።

ከ62ቱ ተሳፋሪዎች መካከል 10ሩ ሕጻናት ሲሆኑ ሁሉም ኢንዶኔዥያውያን ናቸው።

የስሪዊጃያ አየር መንገድ 737-500 የተከሰከሰው ቅዳሜ ከቀትር በኋላ ከመዲናይቱ ጃካርታ ሶካርኖ-ሃታ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አኮብኩቦ በረራ ከጀመረ አሥር ደቂቃዎች በኋላ ነው።

በባለ ስልጣናት በኩል እስካሁን እስካሁን በሕይወት የተረፉ ሰዎች ካሉ በሚል የፍለጋ ተግባራት ላይ ከማተኮር በስተቀር ለአደጋው መንሰኤ ይህ ነው የሚል ምክንያት በይፋ አልተሰጠም።

የጃካርታ ፖሊስ ቃል አቀባይ ዩስሪ ዩኑስ "አንድ የመንገደኛ ዕቃዎችንና ሌላ የአስከሬን አካላትን የያዙ ሁለት ከረጢቶችን" ተረክበናል ብለዋል።

የስሪዊጃያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር SJ182 ከጃካርታ ተነስቶ የ90 ደቃኢቃ በረራውን አቅንቶ የነበረው የኢንዶኔዥያ አካል ወደ ሆነችው ቦርኒዮ ደሴት ነበር።

Amharic News 10 January 2021
This flight path of Indonesian Sriwijaya Air Flight 182 before it dropped off radar, Saturday, Jan. 9, 2021. Source: AP/Flightradar24.com

ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ስለ ቤተሰቦቻቸው ሁኔታ ለማወቅ ፖንቲያናክ አውሮፕላን ማረፊያ ይጠባበቁ ከነበሩት መካከል ያማን ዛይ እያነቡ ሲናገሩ "ከተሳፋሪዎቹ ውስጥ አራቱ የኔ ቤተሰቦች ናቸው። ሚስቴና ሶስት ልጆቼ። ሚስቴ ዛሬ የሕጻኑን ልጃችንን ፎቶግራፍ ልካልኝ ነበር… እንዲህ ባለ ሁነት ልቤ እንደምን ተሰንጥቆ አይበጫጨቅም?" ሲሉ በኃዘን ተመልተው ተናግረዋል።

Amharic News 10 January 2021
Relatives of passengers arrive at a crisis centre at Soekarno-Hatta International Airport in Tangerang. Source: AP

 


1 min read

Published

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now