ከ65 ሺህ ዓመታት በላይ የአውስትራሊያ ሰፋሪና ባላገርነት ከኖቬምበር 8 - 15 ታስቦ በሚከበርበት የብሔራዊ ነባር ዜጎች (NAIDOC) ሳምንት ውስጥ የነባር ዜጎች ሰንደቅ ዓላማ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ውስጥ እንዲቆም የቀረበውን ጥያቄ የፌዴራል መንግሥቱ የእምቢታ ድምፅ በመስጠት ውድቅ አድርጎታል።
የነባር ዜጎች ሰንደቅ ዓላማ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ውስጥ ከአውስትራሊያ ሰንደቅ ዓላማ ጎን እንዲቆም ዕሳቤውን ዛሬ ዕለተ ማክሰኞ ያቀረቡት ከሌበር ፓርቲ ወገን ፓት ዶድሰንና ማላንዳሪ ማክካርቲ እንዲሁም ከግሪንስ ፓርቲ በኩል ሊዲያ ቶርፕ ናቸው።
ዕሳቤው 29 ለ28 በሆነ ውድቅ ሆኗል።
የቤተሰብና ማኅበራዊ ግልጋሎቶች ሚኒስትር አን ራስተን "መንግሥት የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ውስጥ ሊውለበለብ የሚገባው ብቸኛው ተገቢ ሰንደቅ ዓላማ ሁሉንም አውስትራሊያውያንን የሚወክለው የአውስትራሊያ ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ብቻ ነው ብሎ ያምናል" ብለዋል።

"የነባር ዜጎች ሰንደቅ ዓላማም ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ነው" የያንዩዋዋ ሴት ሴናተር ማላንዲሪ ማክካርቲ አያይዘውም "በተሰረቀ መሬት ላይ ያለን መሆናንችንን ሁላችሁንም ልብ ላሰኝ እችላለሁ? የነባር ዜጎች ሰንደቅ ዓላማ በዓለም ላይ አንጋፋና ቀጣይ ባሕልን የሚወክል ነው"

“የኔ ሰዎች … ለሺህና ሺህ ትውልዶች እዚህ አሉ። የነባር ዜጎች ሰንደቅ ዓላማ እኛን ገላጭና የተቆራኘንበት ነው" በማለት ምላሽ ሰጥተዋል።

