ቭላድሚር ፑቲን ለፍንዳታ በተዳረገው የክራሚያ ድልድይ ሳቢያ ዩክሬይንን በ 'ሽብርተኝነት' ፈረጁ

28 የአውስትራሊያ መከላከያ ፕሮጄክቶች በ97 ዓመታት ወደ ኋላ ቀርተዋል ተባለ

A truck bomb on Saturday ignited a massive fire on the road and rail link between Russia and the annexed Crimea peninsula, killing three people.jpg

A truck bomb on Saturday ignited a massive fire on the road and rail link between Russia and the annexed Crimea peninsula, killing three people. Credit: Getty / GAVRIIL


የሩስያ ፕሬዚደንት ቭላድሚር ፑቲን ለክራሚያ ድልድይ መጋየት የዩክሬይን የምስጢር አገልግሎቶች እጅ አለበት ሲሉ ከሰሱ።

አቶ ፑቲን ሩስያንና ዩክሬይንን የሚያገናኘውን ድልድይ ላይ ጉዳት በማድረስ ዩክሬይን "በሽብር ድርጊት" ተሳትፋለች ብለዋል።

አያይዘውም "ለዚህ ምንም ጥርጥር የለውም። ይህ ጠቀሜታው ወሳኝ የሆነን የሰላማዊ ሰዎች መሠረተ ልማትን ለማውደም ያለመ የሽብር ድርጊት ነው

"የተተለመው፣ ትዕዛዝ የተሰጠውና የተተገበረው በዩክሬይን ልዩ አገልግሎቶች ነው" ብለዋል።



ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ እሑድ ዕለት የተወነጨፈው የሩስያ ሚሳይል ጥቃት በዩክሬይን ደቡባዊ ምሥራቅ ከተማ በሆነችው ዛፖሪዝሂያ በሚገኝ አንድ አፓርትመንት ህንፃ ላይ ወድቆ የ13 ሰዎች ሕይወት ማለፉንና 89 ለመቁሰል አደጋ መዳረጋቸውን የዩክሬይን ባለስልጣናት አስታውቀዋል።

መከላከያ

የአውስትራሊያ መከላከያ ሚኒስትር ሪችድ ማርልስ የተወሰኑ የመከላከያ ፕሮጄክቶች ጊዜ ያለፋባቸው በመሆንና በዋጋቸው አለቅጥ መናር ሳቢያ ከእነ አካቴው ሊሰረዙ እንደሚችሉ አመላከቱ።

 በያዝነው የወርኅ ኦክቶበር አዲስ የበጀት ትንተና መሠረት 28 የመከላከያ ፕሮጄክቶች በጋራ 97 ዓመታት ወደ ኋላ ቀርተዋል፤ 18 ፕሮጄክቶች ዋጋቸው በ6.5 ቢሊየን ዶላርስ አሻቅቦ ተገኝቷል።

በመሆኑም፤ የተወሰኑ ፕሮጄክቶች ሊታጠፉ እንደሚችሉና የመከላከያ ስትራቴጂ ክለሳ በሂደት ላይ ስለመሆኑ የመከላከያ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።

 




Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service