በዛሬው ዕለት ማክሰኞ ቪክቶሪያ ውስጥ የ19 ሰዎች ሕይወት በኮሮናቫይረስ ሲያልፍ 331 በቫይረሱ ተጠቅተዋል።
ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ሕይወታቸው ካለፈው ውስጥ አንዲት ሴት በ50ዎቹ፣ አንድ ወንድ በ70ዎቹ ፣ ስድስት ሴቶችና አራት ወንዶች በ80ዎቹ፣ አራት ሴቶችና ሶስት ወንዶች በ90ዎቹ ዕድሜ የነበሩ ናቸው።
ከ19ኙ ሟቾቹ ውስጥ 14ቱ በአረጋውያን መጦሪያ ነዋሪ የነበሩ ናቸው።
ቪክቶሪያ ውስጥ በኮሮናቫይረስ የ19 ሰዎች ሲጠፋ የዛሬው ሁለተኛ ጊዜ ነው። ይህም ቪክቶሪያ ውስጥ ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎችን ቁጥር ወደ 246 ሲያደርስ በአገር አቀፍ ደረጃ 331 ደርሷል።
የሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሰት አፋር ውስጥ በደረሰው የተፈጥሮ ጎርፍ አደጋ ለተጎዱ ነዋሪዎች የጤና ባለሙያዎችን አክሎ የተለያዩ እርዳታዎችን በዓይነት ልኳል።
የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ እንዳስታወቀው 300 ካርቶን የምግብ ዘይት፣350 ኩንታል ዱቄት፣566 ኩንታል ሩዝ 620 ብርድ ልብሶችና 520 የዝናብ መከላከያ ሸራዎች ለተጎዱ ወገኖች መርጃ ተልኳል።

