ቪክቶሪያ የ2026 የጋራ ብልፅግና ጨዋታዎችን ለማስተናገድ በጋራ ብልፅግና ፌዴሬሽን ተመረጠች።
ዝግጅቶቹ በአብዛኛው በሪጂናል ቪክቶርያ የሚካሔዱ ይሆናል።
የቪክቶሪያ ፕሪሚየር ዳንኤል አንድሩስ የስፖርት ውድድሮቹ ቤንዲጎ፣ ባላራት፣ ጂሎንግ እና ጊፕስላንድ እንደሚከናወኑ ገልጠዋል።
እንዲሁም ዋነኛ ስፖርታዊ ውድድሮች፣ የሥነ ሥርዓቱ መክፈቻና መዝጊያዎች ሜልበር ውስጥ ይካሄዳሉ።
ሥራ ፈጠራ
ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት 1.3 ሚሊየን የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር ማቀዳቸውን ገለጡ።
የአቶ ሞሪሰን ጥምር መንግሥት የፍብረካ፣ የእጅ ሙያ የሥራ ቦታ ስልጠናና ክህሎትን ማሳደግ ላይ እንደሚያተኩር አመላክቷል።

የሥራ አጥነት መጠን በዚህ ዓመት መጨረሻ ወደ 3.75 ፐርሰንት ዝቅ እንደሚል ይጠበቃል።
አቶ ሞሪሰን አሁን ተከስቶ ያለውን የሠራተኞችን እጥረት ለመቅረፍ ተጨማሪ ሠራተኞች ከባሕር ማዶ እንዲመጡ በር ይከፍቱ እንደሁ ተጠይቀው፤ በጀት ውስጥ ከሠፈረው 160,000 በላይ ተጨማሪ ባሕር ማዶኞች ወደ አውስትራሊያ እንዲዘልቁ እንደማይደረግ ተናግረዋል።
የቴሌጤና ፕሮግራም
የአውስትራሊያ ሌበር ፓርቲ በገጠራማ አውስትራሊያ ለሚኖሩ አውስትራሊያውያን በያዘው የጤና ፕሮግራም መሠረት የስነ አዕምሮ ግልጋሎት እንዲያገኙ የቴሌጤና ፕሮግራም ማካሄጃ የሚውል 31 ሚሊየን ዶላርስ መመደቡን የተቃዋሚ ቡድን መሪ አቶ አንቶኒ አልባኒዚ ዛሬ ታዝማኒያ ባካሄዱት የምርጫ ዘመቻ ወቅት አስታውቀዋል።

አያይዘውም፤ የቴሌጤና ፕሮግራሙ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት የነበረውን የ50 ፐርሰንት ድጎማ የሞሪሰን መንግሥት በመክላቱ ያንን ክፍተት ለሟሟላትና ግልጋሎቶቹን በርካሽ ማካሔድ እንዲያስችል ለማድረግ መሆኑን ገልጠዋል።
በሚቀጥሉት አራት ዓመታት ውስጥ 450,000 አውስትራሊያውያን የቴሌጤና ግልጋሎቶች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ጥናቶች የሚያመልክቱ እንደሆነም አቶ አልባኒዚ አስረድተዋል።

