ባለፉት 24 ሰዓታት ቪክቶሪያ ውስጥ 37 ሰዎች በኮሮናቫይረስ ሲጠቁ ስድስት ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።
በቫይረሱ የተጠቁት ሰዎች ቁጥር ከጁን 25 ወዲህ ዝቅተኛው ነው።
ይህም የ14 ቀናቱን አማካይ የቫይረስ መጠን በሜልበርን 61.6 በሪጂናል ቪክቶሪያ 4.3 እንዲደርስ ማድረጉን ፕሪሚየር ዳንኤል አንድሩስ ተናግረዋል።
ስድስቱም ሕይወታቸውን በቫይረሱ ሳቢያ ያጡት የአረጋውያን መጦሪያ ነዋሪዎች የነበሩ ሲሆን፤ ሁለት ሴቶችና አንድ ወንድ በ80ዎቹ፣ ሁለት ሴትና ስንድ ወንድ በ90ዎቹ ዕድሜ ውስጥ የነበሩ ናቸው።
ተጨማሪው ሞት ቪክቶሪያ ውስጥ በቫይረሱ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 716 አድርሷል።
በአሁኑ ወቅት በኮቪድ-19 ተይዘው ያሉ 1251 ሲሆኑ 126 ሆስፒታል ተኝተው የሚታከሙ፣ ዘጠኝ ፅኑ ሕሙማን ክፍሎች ሕክምና የሚከታተሉና ስድስት በሰው ሠራሽ መተንፈሻ እየተነፈሱ ያሉ ናቸው።
ምርጫ
በትግራይ ክልል ጳጉሜን 4 በተካሔደው ክልላዊ ምርጫ ሕወሓት አሸናፊ መሆኑን የክልሉ ምርጫ ኮሚሽን አስታውቋል።
በውጤቱም፤
ሕወሓት - 98.2 %
ባይቶና - 0.8 %
ውናት - 0.71 %
ሳወት - 0.27 %
አሲምባ - 0.0.1 % ድምፅ ማግኘታቸውን የትግራይ ምርጫ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሉወርቅ ኪዳነማርያም ለብዙሃን መገናኛ ገልጠዋል።

