ቪክቶሪያ ውስጥ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ 278 ሰዎች በኮሮናቫይረስ ሕይወታቸውን ሲያጡ ስምንት ለሞት ተዳርገዋል።
በትናንትናው ዕለት ቪክቶሪያ የ21 ሰዎቿን ሕይወት ስታጣ 410 በኮሮናቫይረስ ተጠቅተውባታል።
የዛሬው ቁጥር ከጁላይ 20 ወዲህ አዲስ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር አሽቆልቁሎ የታየበት ነው።
የስምንቱ ስዎች ሕልፈተ ሕይወት የቪክቶሪያን በቫይረሱ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 275 ሲያደርሰው አገር አቀፉን ወደ 360 ከፍ አድርጎታል።
ፕሪሚየር ዳንኤል አንድሩስ በዛሬው ዕለት ሕይወታቸውን በኮሮናቫይረስ ያጡቱ ስምንቱ ሰዎች የአረጋውያን መጦሪያ ነዋሪዎች እንደነበሩ ገልጠዋል።
አያይዘውም፤ ከሟቾቹ ውስጥ አንዲት ሴት በ50ዎቹ፣ ሁለት ወንዶች በ70ዎቹ፣ ሁለት ሴቶች በ80ዎቹ፣ ሁለት ወንዶች በ80ዎቹ እንዲሁም አንድ ወንድ በ90ዎቹ የነበሩ መሆኑን አስታውቀዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ ኢትዮጵያ ውስጥ እስከ ነሐሴ 6 - 20212 በነበሩት 24 ሰዓታት ውስጥ 943 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ 23 ሕይወታቸው አልፏል።
በአሁኑ ወቅት በአገር አቀፍ ደረጃ በኮሮናቫይረስ ተጠቅተው ያሉ ሰዎች ቁጥር 13 ሺህ 619 ደርሷል። 463 ሕይወታቸውን አጥተዋል።
በጠቅላላው በቫይረሱ ተይዘው ከነበሩት 25 ሺህ 118 ሰዎች ውስጥ 11 ሺህ 34 አገግመዋል።
Share

