የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 4ኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ሥርዓተቀብር የቤተክርስቲያኗ ሥርዓተ ቀኖና በሚያዘው መልኩ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል።

በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴደራል በተከናወነው የቀብር ሥነ-ሥርዓት ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፣ ክብርት ሣህለወርቅ ዘውዴ የኢፌድሪ ፕሬዚደንት፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ካህናት አባቶች፣ የ አብያተ ክርስቲያናት ተወካዮች እና በርካታ ሕዝብ ክርስቲያን ምዕመናን ተገኝተዋል።
Share

