ትናንት ጥቅምት 2 በኬንያ - ናይሮቢ በተከናወነው የምሥራቅ አፍሪካ አገራት የፊልም ጥበብ ተማሪዎች የምርቃት ሥነ ሥርዓት ነው አሸናፊነቱ ይፋ የተደረገው።
መልቲቾይዝ ታለንት ፋክተሪ ለአንድ ዓመት ለወጣት የፊልም ባለሙያዎች የሚሰጥ ስኮላርሺፕ ሲሆን፤ በስልጠናና የተግባር ትምህርት ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ምሩቃን ወደ ኒውዮርክ፣ ቦሊውድና ደቡብ አፍሪካ ለላቀ ከፍተኛ ትምህርት የሚጓዙበትን ሽልማት ያሸንፋሉ።

ኢትዮጵያዊው መልካሙ ኃይሌ አንደኛ በመውጣቱ ኒውዮርክ የሚጓዝ ሲሆን የኬንያ እና የታንዛኒያ ምሩቃን ወደ ሕንድ ቦሊውድና ወደ ደቡብ አፍሪካ ይጓዛሉ።
ከምስራቅ አፍሪካ አገራት ከተውጣጡ 19 ምሩቃን መካከል ሁለት ኢትዮጵያውያን ወጣት የፊልም ባለሙያዎች በኬንያ ናይሮቢ የፊልም ጥበብ ሲማሩ ቆይተዋል።
[ ደመቀ ከበደ ፡ ናይሮቢ ኬንያ ]

