ጠቅላይ ሚኒስትር አልባኒዚ ኤርትራዊት-አውስትራሊያዊቷን ሳባ አብርሃምን ጨምሮ በንግሥት ኤልሳቤጥ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ አብረዋቸው የሚታደሙ 10 አውስትራሊያውያንን መረጡ

አሥሩ አውስትራሊያውያን በዳግማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ለመገኘት ወደ ለንደን የሚያቀኑት ከጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚና ጠቅላይ እንደራሴ ዲቪድ ሃርሌይ ጋር ነው።

King Charles III attend a Service of Prayer and Reflection for the Life of Queen Elizabeth II at St Giles' Cathedral.jpg

King Charles III attend a Service of Prayer and Reflection for the Life of Queen Elizabeth II at St Giles' Cathedral, on September 12, 2022 in Edinburgh, Scotland. Credit: Jane Barlow - WPA Pool/Getty Images

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ በዳግማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ አብረዋቸው የሚታደሙ 10 አውስትራሊያውያንን መምረጣቸውን አስታወቁ።

አሥሩ አውስትራሊያውያን ለንግሥቲቱ የቀብር ሥነ ሥር ዓት ላይ የሚገኙት ባኪንግሃም ቤተመንግሥት ከርዕሰ መንግሥትና ርዕሰ ብሔሩ በተጨማሪ 10 የአውስትራሊያን ባሕልና ዕሴቶችን የሚያንፀባርቁ አውስትራሊያውያንም አብረው እንዲታደሙ በላከው ግብዣ መሠረት ነው።

በዚሁም መሠረት የ2022 የዓመቱ አውስትራሊያዊ ዲላን አልኮትንና የ2022 የኩዊንስላንድ የአካባቢ ጀግና ሽልማት ተሸላሚዋን ሳባ አብረሃምን አክሎ 10 የማኅበረሰብ አባላት አውስትራሊያውያንን ወክለው በቀብሩ ሥነ ሥርዓት ላይ ይታደማሉ።

አሥሩ አውስትራሊያውያን በዳግማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥ የቀብር ሥነ ሥ ርዓት ላይ ለመገኘት ወደ ለንደን የሚያቀኑት ከጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚና ጠቅላይ እንደራሴ ዲቪድ ሃርሌይ ጋር ነው። በለንደን የአውስትራሊያ ተጠባባቂ ከፍተኛ ኮሚሽነር ሊኔት ውድ ከመሪዎቹና የማኅበረሰብ አባላቱ ተወካዮች ጋር በጋራ ይታደማሉ።


1 min read

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now