የአውስትራሊያ ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትር ሪችድ ማርልስ የቻይናና ታይዋን ውጥረት ከረገበ ዓለም "የእፎይታ ትንፋሽ' እንደምትተነፍስ ተናገሩ።
ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስትራሊያ በቻይናና ታይዋን ጉዳይ የምታካሂደው ውይይት ፕሮፌሽናል፣ ስክነትና ዲፕሎማሲን የተላበሰ እንደሚሆን ገልጠዋል።
በታይዋን ባሕረ ሰላጤ ዙሪያ ውጥረቶችን ያስፈነው የቻይና ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን ማድረግ ሲሆን፤ አስባቡም የዩናይትድ ስቴትስ አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ነው።
የቻይናን ጦር ቦለስቲክ ሚሳይሎችን እስከማስወንጨፍ የደረሰው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ማብቃቱን የቻይና ምሥራቅ ዕዝ ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
አቶ ማርልስ አውስትራሊያ ከቻይና ጋር የሰከነ ግንኙነትን ማድረግ እንደምትሻ ጠቁመዋል።
.
***
የሕወሓት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ፤ ድርጅታቸው ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር "ቀጥተኛ ግንኙነቶችን" አድርጓል ተብሎ መዘገቡን አስተባበሉ።
ቃል አቀባዩን ማስተባባያ ለመስጠት ግድ ያሰኘው AFP 'በትግራይ አማፅያንና በኢትዮጵያ መንግሥት" በኩል የቀጥታ ግንኙነት እንደተካሔደ የአፍሪካ ኅብረት መግለጫ ዋቤ አድርጎ መግለጡን ተከትሎ ነው።
አቶ ጌታቸው ሪፖርቱን በፍብረካነት ኮንነው 'ከቶውንም ያልሆነ' ሲሉ በቲዊተር ገፃቸው አሌ ብለውታል።

