የአውስትራሊያ ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትር የቻይናና ታይዋን ውጥረት ከረገበ ዓለም 'የእፎይታ ትንፋሽ' እንደሚተነፍስ ገለጡ

ሕወሓት ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አለማድረጉን አስታወቀ

Acting Prime Minister Richard Marles.jpg

Acting Prime Minister Richard Marles hopes for a de-escalation in the Taiwan Strait. Credit: AAP / Jono Searle

የአውስትራሊያ ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትር ሪችድ ማርልስ የቻይናና ታይዋን ውጥረት ከረገበ ዓለም "የእፎይታ ትንፋሽ' እንደምትተነፍስ ተናገሩ።

ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስትራሊያ በቻይናና ታይዋን ጉዳይ የምታካሂደው ውይይት ፕሮፌሽናል፣ ስክነትና ዲፕሎማሲን የተላበሰ እንደሚሆን ገልጠዋል።

በታይዋን ባሕረ ሰላጤ ዙሪያ ውጥረቶችን ያስፈነው የቻይና ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን ማድረግ ሲሆን፤ አስባቡም የዩናይትድ ስቴትስ አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ነው።

የቻይናን ጦር ቦለስቲክ ሚሳይሎችን እስከማስወንጨፍ የደረሰው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ማብቃቱን የቻይና ምሥራቅ ዕዝ ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

አቶ ማርልስ አውስትራሊያ ከቻይና ጋር የሰከነ ግንኙነትን ማድረግ እንደምትሻ ጠቁመዋል።
.
***

የሕወሓት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ፤ ድርጅታቸው ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር "ቀጥተኛ ግንኙነቶችን" አድርጓል ተብሎ መዘገቡን አስተባበሉ።

ቃል አቀባዩን ማስተባባያ ለመስጠት ግድ ያሰኘው AFP 'በትግራይ አማፅያንና በኢትዮጵያ መንግሥት" በኩል የቀጥታ ግንኙነት እንደተካሔደ የአፍሪካ ኅብረት መግለጫ ዋቤ አድርጎ መግለጡን ተከትሎ ነው።

አቶ ጌታቸው ሪፖርቱን በፍብረካነት ኮንነው 'ከቶውንም ያልሆነ' ሲሉ በቲዊተር ገፃቸው አሌ ብለውታል።


Share

Published

Updated

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
የአውስትራሊያ ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትር የቻይናና ታይዋን ውጥረት ከረገበ ዓለም 'የእፎይታ ትንፋሽ' እንደሚተነፍስ ገለጡ | SBS Amharic