የጎንደር ድል የአርበኞች መታሰቢያ ሐውልቶች በጎንደርና ሎንዶን ሊቆሙ ነው

የጎንደር ድል ኢትዮጵያውያን አርበኞች በሁለተኛው የዓለም ጦርነት 1941 / 1934 የጣሊያንን ሠራዊት ድል የነሱበትና የእንግሊዝና የጋራ ብልፅግና ጦር አባላት በአጋርነት የተሳተፉበት ዝክረ መታሰቢያ ነው።

HIH Prince Ermias Sahle Selassie Haile selassie.jpg

HIH Prince Ermias Sahle-Selassie Haile-Selassie. Credit: SBS Amharic

ኢትዮጵያውያን አርበኞች ዳግም የጣሊያን ወረራን በ1941 / 1934 በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አመራር ድል የነሱበትና የእንግሊዝ ጦር በአጋርነት የተሳተፈበትን ድል በክብር ለመዘከር በጎንደርና ሎንዶን ከተሞች የመታሰቢያ ሐውልቶች ሊቆሙ ነው።

የመታሰቢያ ሐውልቶቹ በኢትዮጵያና እንግሊዝ ከተሞች ለማቆም መታቀዱን የገለጠው የኢትዮጵያ የዘውድ ምክር ቤት ሲሆን፤ በመጪው ዓመት የመጀመሪያው ሎንዶን ላይ የሚቆመው ሐውልት በክብር ተመርቆ ይፋ የሚሆነው በምክር ቤቱ ፕሬዚደንት ልዑል ኤርሚያስ እንደሚሆንና አንድ ወይም ከዚያ በላይ የእንግሊዝ ከfተኛ ባለስልጣን በሥፍራው እንደሚገኙ ተመልክቷል።  

ጎንደር ላይ የሚቆመው ሁለተኛው ሐውልትም በልዑል ኤርሚያስ ተመርቆ እንደሚከፈትና በሥፍራውም የኢትዮጵያ፣ እንግሊዝና የጋra ብልፅግና ከፍተኛ ባለስልጣናት እንደሚገኙ ተነግሯል።

በቅርቡም በአቀራረፁ ላይ ዳግማዊ ንግሥት ኤልሳቤጥ የተሳተፉበትና የኢትዮጵያውያን አርበኞችን፣ የእንግሊዝና የጋራ ብልፅግና ጦር አባላትን የሚዘክር "የጎንደር ድል" የክብር ሜዳል በዘውድ ምክር ቤቱ ተቀርፆ ለሽልማትነት በቅቷል።

 


1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now