ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ ይቋረጣል ተብሎ የታሰበው የወረርሽኝ የሥራ ፈቃድ ክፍያ እንደሚቀጥል አስታወቁ

*** ሩስያና ዩናይትድ ስቴትስ የዩክሬይን ጦርነት ውጥረትን ወደ ጎን ብለው ጠፈርተኞቻቸው ወደ ሕዋ አብረው እንዲመጥቁ ከስምምነት ላይ ደረሱ

Le journal du 16/07/2022

Anthony Albanese. Source: Getty Images

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ ይቋረጣል ተብሎ የታሰበው የወረርሽኝ የሥራ ፈቃድ ክፍያ እንደሚቀጥል አስታወቁ። 

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሠራተኛ ማኅበራትና የረድኤት ድርጅቶችን ጥሪ ተከትሎ የፌዴራል መንግሥቱ የ $750 የወረርሽኝ የሕክምና ፈቃድ ክፍያ መቀጠልን ያስታወቁት ዛሬ ከቀትር በኋላ በጠሩት ጋዜጣዊ መግለጫቸው ወቅት ነው።   

ቀደም ሲል የፌዴራል መንግሥቱ ከቀድሞው መንግሥት የተጫነበት ከአንድ ትሪሊየን ዶላር በላይ ዕዳ ያለበት በመሆኑ በክፍያው ለመቀጠል እንደሚያውከው አመላክቶ ነበር። 

ሆኖም የኩዊንስላንድ መንግሥት በጠራው አስቸኳይ የብሔራዊ ካቢኔ ስብሰባ ላይ የተመከረበት በኮቪድ-19 የተጠቁ ሠራተኞች ከሥራ ገበታ በሚቀሩበት ወቅት ክፍያ እንዲያገኙ ለማስቻል የፌዴራልና የክፍለ አገራት መንግሥታት የወጪውን እኩሌታ በመጋራት ለመሸፈን ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።

የአስቸኳይ ጊዜ የድጋፍ ክፍያው የሚዘልቀው እስከ ወርሃ ሴፕቴምበር መጨረሻ ይሆናል። 

የጠፈር ጉዞ

ሩስያና ዩናይትድ ስቴትስ በዩክሬይን ጦርነት ሳቢያ በመካከላቸው የተፈጠረውን ጆኦፖለቲካዊ ውጥረት ወደ ጎን ብለው ከዓለም አቀፍ የጠፈር ጣቢያ በጋራ ለመምጠቅ ከስምምነት ላይ ደረሱ። 

በስምምነቱም መሠረት የዩናይትድ ስቴትስ ጠፈርተኞች ወደ ሩስያ ተጉዘው በሩስያ ሶዩዝ የሕዋ መንኮራኩር የሚጓዙ ሲሆን፤ የሩስያ ጠፈርተኞችም ወደ ዩናይትድ ስቴትስ አምርተው ከፍሎሪዳ በምትመጥቀው ሕዋ ኤክስ ሮኬት ተጓዥ ይሆናሉ።  

 

 


Share

Published

By NACA
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service