የምዕራብ አውስትራሊያ ፖሊስ ለአውስትራሊያ ዜግነት የሚያበቃ ዓለም አቀፍ የፖሊስ ሠራዊት አባላት ምልመላ ዘመቻ ጀመረ።
ምልመላው አተኩሮ ያለው ከአውስትራሊያ ጋር ተመሳሳይ የፖሊስ አሠራር ካላቸው አገራት እንግሊዝ፣ አየርላንድና ኒውዝላንድ ላይ ነው።
ከመመዘኛዎቹም ውስጥ የሶስት ዓመታት የፖሊስ ሥራ ልምድና ዕድሜያቸው ከ55 ዓመት በታች ሊሆን እንደሚገባ የምዕራብ አውስትራሊያ ፖሊስ ኮሚሽነር ገልጠዋል።
የምዕራብ አውስትራሊያ ፖሊስ ሚኒስትር ፖል ፓፓሊያ የባሕር ማዶው ምልመላ በመላው አውስትራሊያ የሚካሔደው ምልመላ አንዱ አካል እንደሆነ አመልክተዋል።
የማክጋዋን መንግሥት ከ1,000 በላይ የፖሊስ ሠራዊት ለመቅጠር አልሟል።
የጎርፍ ማስጠንቀቂያ
በምሥራቃዊ ክፍለ አገራት በተለይም ቪክቶሪያ እና ኒው ሳውዝ ዌይልስ ላይ የጎርፍ ማስጠንቀቂያው ፀንቶ አለ።
የቪክቶሪያ ጉልበርን ወንዝ፣ የማዕከላዊ ሰሜን ቪክቶሪያ ሼፐርተን፣ ሲሞርና ማርቺሰን ከፍተኛ የጎርፍ ማስጠንቀቂያ ተሰTቶባቸዋል።
ለበርካታ ነዋሪዎች ቀዬአቸውን ለቅቀው ለመውጣት በእጅጉ የዘገዩ መሆኑ የተመለከተ ሲሆን፤ የቪክቶሪያ ፖሊስ ረዳት ኮሚሽነር ዴቪድ ክሌይተን ነዋሪዎች ማስጠንቀቂያዎችን ግብር ላይ ማዋሉ በእጅጉ ጠቃሚ እንደሆነ አሳስበዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ ኒው ሳውዝ ዌይልስ በደቡብ ሪቬሪና ሪጂን ናሬንዴራ እና በማዕከላዊ ምዕራብ ኒው ሳውዝ ዌይልስ ፎርብስ ቀዬዎቻቸውን ለቅቀው እንዲወጡ ትዕዛዞች ተላልፈዋል።