የፌዴራል መንግሥቱ ሜይ 21 በሚካሔደው ምርጫ በለስ ቀንቶት ዳግም ከተመረጠ አን ራስተን የጤናና የአረጋውያን ክብካቤ ሚኒስትር እንደሚሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ዛሬ እሑድ ኤፕሪል 17 አስታወቁ።
ሴናተር ራስተን በአሁኑ ወቅት የማኅበራዊ አገልግሎቶች ሚኒስትር ሲሆኑ፤ ተተኪነታቸው ከፖለቲካው ዓለም በሚገለሉት ግሬግ ሃንት ፈንታ ነው።
አቶ ሞሪሰንና አቶ ሃንት በዛሬው ዕለት ለዓይነት አንድ ስኳር በሽታ ግሉኮስ መቆጣጠሪያ ፕሮግራም ማስፋፊያ የሚውል በሊብራል/ናሽናልስ ፓርቲ በኩል መመደቡን ይፋ አድርገዋል።
የሴናተር ራስተንን የጤና ሚኒስትርነት ስየማ ተከትሎ የሌበር ፓርቲ መሪ አንቶኒ አልባኒዚ፤ ስየማው የሚያመልክተው የሞሪሰን መንግሥት ዳግም ከተመረጠ የሜዲኬር በጀተ ቅነሳ እንደሚገጥመው ማመላከቻ ነው በማለት ትችትና ማሳስቢያ ሰንዘረዋል።
ለአቶ አልባኒዚ ትችት ሰበቡ፤ ወ/ሮ ራስተን በ2015 'ሜዲኬርን አሁን ባለበት ሁኔታ ደጉሞ መዝለቅ አዋኪ ነው' ሲሉ በሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ቤት ንግግር ከማድረጋቸው ጋር የተያያዘ ነው።
ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ የአውስትራሊያ ምርጫ ኮሚሽን አሳሳች የፖስታ ድምፅ መስጫ ማመልከቻ ቅፅን አስመልክቶ ለፖለቲካ ፓርቲዎች የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ልኳል።
ኮሚሽኑ አሳሳች ቅፆች ለመራጮች የመላካቸውን ሪፖርት ነቅሶ፤ የኮሚሽኑን ሐምራዊ ቀለም የተላበሱ ቅፆች መላካቸውን ጠቅሷል።
ድርጊቱ አሳሳች ብቻም ሳይሆን ሕገ ወጥ መሆኑንም አሳስቦ አስጠንቅቋል።

