ኢትዮጵያና ሩስያ ወታደራዊ ስምምነት አደረጉ

***የአውሮፓ ኅብረት የውጭ ጉዳዮች ዋና የፖሊሲ ኃላፊ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ኢትዮጵያ ላይ ማዕቀብ ለመጣል እንዲቻል አሳሰቡ

SBS Amharic

Source: SBS Amharic

ኢትዮጵያና ሩሲያ በወታደራዊ ቴክኒክ መስክ ተባብረው ለመሥራት ጁላይ 12, 2021 ስምምነታቸውን በፊርማ አፀደቁ።

በሁለቱ አገራት መካከል የተካሔደውን የስምምነት ፊርማ በኢትዮጵያ በኩል ያኖሩት የመከላከያ ሚኒስቴር ፋይናንስ ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ማርታ ሊዊጅ ናቸው።

ከስምምነቱ ላይ የተደርሰውም በኢትዮጵያና ሩስያ ተወካዮች ሶስት ቀናት ይየፈጀው የጋራ ውይይት እንዳበቃ ነው። 

የወታደራዊ ቴክኒክ ስምምነቱ "የሠራዊትቱን አቅም በዕውቀት፣ በክህሎትና ቴክኖሎጂ ለመገንባት ለሚደረገው ጥረት ፋይዳው የጎላ" መሆኑን ሚኒስትር ደኤታዋ ለአገር ውስጥ ጋዜጠኞች ገልጠዋል።  

ማዕቀብ የአውሮፓ ኅብረት

የአውሮፓ ኅብረት የውጭ ጉዳዮች ዋና የፖሊሲ ኃላፊ ጆሴፕ ቦሬል አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ኢትዮጵያ ላይ ማዕቀብ መጣል እንዲቻል ለኅብረቱ አገራት አሳሰቡ።

አቶ ቦሬል ትግራይ ውስጥ ያለው ሁኔታ እየከፋ ያለ መሆኑን ጠቅሰው ሁኔታዎች አሳማኝ ሆነው ሲገኙ የማዕቀብ እርምጃዎችን ለመውሰድ የኅብረቱ አገራት ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው ተናግረዋል።
European Union foreign policy chief Josep Borrell.
European Union foreign policy chief Josep Borrell. Source: Getty
አክለውም "ምንም እንኳ በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል የተኩስ ማቆም ዕወጃ ቢደረግም፤ ትግራይ ውስጥ እያየን ያለነው፤ ስጋት አድሮብን ያለው ትግራይ ብርቱ ሰብዓዊ ቀውስ እንደሚገጥማት ነው" ብለዋል።

ቦሬል ይህን የተናገሩት ጁላይ 12 ብራስልስ ውስጥ የተካሔደው የአውሮፓ ኅብረት የውጭ ጉዳዮች ምክር ቤት ስብሰባ አብቅቶ በጋራ በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።  

የኢትዮጵያ መንግሥት ጁን 28 የተናጠል ተኩስ ማቆም ዕወጃ ማድረጉና መቀሌን ለቅቆ መውጣቱ ይታወሳል። 

 


Share

1 min read

Published

Updated

By Stringer Report


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service