የልዑል ፊሊፕ የመጨረሻ ስንብት

*** ከስድስት መቶ ሺህ በላይ የኢትዮጵያ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ሃብትና ንብረቶች ምዝገባ ተካሄደ

Queen Elizabeth

Queen Elizabeth bade farewell to Prince Philip at a funeral on Saturday that celebrated his seven decades of service. Source: Getty

ዳግማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥ ትናንት ቅዳሜ ኤፕሪል 9 ሕይወታቸው ያለፈውን ባለቤታቸውን ልዑል ፊሊፕን በቀብር ሥነ ሥርዓታቸው ላይ ተገኝተው ተሰናበቱ።

በኮሮናቫይረስ መስፋፋት ሳቢያ የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት 30 ለቀስተኞች ብቻ ሲሆኑ፤ ዊንድሶር ቤተመንግሥት ውስጥ በሚገኘው የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ውስጥ የተካሄደው የለቅሶው ሥነ ሥርዓት ለ50 ደቂቃዎች ተካሂዷል።

የ94 ዓመቷ ንግሥት ከባለቤታቸው ሕልፈተ ሕይወት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባባይ ጥቁር የኃዘን ልብስና ጥቁር ይርፊት ጭምብል አጥልቀው ታይተዋል።

Queen Elizabeth II
Queen Elizabeth II during the funeral of Prince Philip, Duke of Edinburgh. Source: UK Press

የቅርብ የቤተሰብ አባላትም በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ ታድመዋል።

Philip
Philip -- described by royals as "the grandfather of the nation" -- was Britain's longest-serving royal consort. Source: Getty

የስነ-ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን

ከ600 ሺህ በላይ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ሃብትና ንብረታቸው ማስመዝገባቸውን የፌዴራል የስነ-ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን አስታወቀ።

ባለፉት ዘጠኝ ወራት የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች የሃብት ምዝገባ መከናወኑን የፌዴራል የስነ-ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ወዶ አጦ ገልጠዋል።

ኮሚሽኑ በዕቅድ ከያዘው 95 በመቶውን ማሳካት እንደቻለ መግለጹን ኢዜአ ዘግቧል።

 


1 min read

Published

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now