ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ ለመጀመሪያ ጊዜ ከንጉሥ ቻርልስ ሳልሳዊ ጋር ተገናኝተው ሐዘናቸውን በአውስትራሊያውያን ስም ገለጡ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአውስትራሊያን የሪፐብሊክ ንቅናቄ ጉዳይ አላነሱም

Britain's King Charles III (left) sits with Prime Minister Anthony Albanese as he receives realm prime ministers in the 1844 Room at Buckingham Palace in London.jpg

Britain's King Charles III (left) sits with Prime Minister Anthony Albanese as he receives realm prime ministers in the 1844 Room at Buckingham Palace in London, on Saturday, 17 September 2022. Credit: AAP / AP

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ ከእንግሊዙ ቻርልስ ሳልሳዊ ጋር ለመጀመሪያ ተገናኙ።

አቶ አልባኒዚ የዳግማዊት ኤልሳቤጥ ሕልፈተ ሕይወትን አስመልክተው በአውስትራሊያውያን ስም ሐዘናቸውን ለንጉሥ ቻርልስ ገልጠዋል።

አውስትራሊያውያን ለንግሥቲቱ መልካም አተያይ እንዳላቸው፣ ጥልቅ ሐዘን የተሰማቸው እንደሆነና ለንግሥቲቱ የ70 ዓመታት አገልግሎትም ከፍ ያለ ከበሬታ እንዳለቸው ተናግረዋል።

ይሁንና አቶ አልባኒዚ በሐዘን ላይ ላሉት ንጉሥ ቻርልስ የአውስትራሊያውያንን የሪፐብሊክ ንቅናቄ ጉዳይ  አላነሱም።

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ አውስትራሊያ ከእንግሊዝ ዘውዳዊ ሥርዓት ጋር ትስስሮሿን በጥሳ የሪፐብሊክ ሥርዓት እንድታቆም ከሚሹት የሪፐብሊካን ንቅናቄ ደጋፊዎች አንዱ ናቸው።

ንጉሥ ቻርልስ ከአቶ አልባኒዚ በተጨማሪ የጋራ ብልፅግና አገራት መሪዎች የካናዳውን ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ፣ የኒውዚላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ጃሲንዳ አርደንና የባሃማስ ጠቅላይ ሚኒስትር ፊሊፕ ዴቪስን ተቀብለው አነጋግረዋል።

በሌላም በኩል የእንግሊዟ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊዝ ትረስ ለንግሥት ኤልሳቤጥ ቀብር ሥነ ሥርዓት ለንደን ከሚገኙት የአውስትራሊያና የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትሮችን በገጠር ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

ወ/ሮ ትረስና አቶ አልባኒዚ በሁለቱ አገራት መካክል ስላለው የንግድ ስምምነት አንስተው ተናጋግረዋል።

ሁለቱ አገራት $3.9 ቢሊየን ዶላርስ [[2.3 ቢሊየን ፓውንድስ]] ግምት ያለው የንግድ ውል ተፈራርመዋል።


1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now