የሰሜን ሜልበር የጋርዮሽ መኖሪያ ቤት ነዋሪዎች ወደ ደጅ መውጣት ተፈቀደላቸው

ከሁለት ሳምንታት የኮሮናቫይረስ የቤት ውስጥ ቆይታ ገደብ ወደ ማኅበረሰባዊ ቅልቅል

Amharic  news 19 July, 2020

Source: SBS

በኮሮናቫይረስ ሜልበርን ውስጥ አገርሽቶ መዛመት ሳቢያ የቪክቶሪያ መንግሥት በወሰደው እርምጃ ከጁላይ 4 ጀምሮ ለሁለት ሳምንታት የሰሜን ሜልበር የጋርዮሽ ቤት ነዋሪዎች ለቤት ውስጥ ቆይታ ግድ ተሰኝተው ቆይተዋል።

ከትናንት ቅዳሜ ማታ ጀምሮ ጥብቅ ገደቡ የላላላቸው የ33 አልፍሬድ ጎዳና ነዋሪዎች እንደተቀሩት ሜልበርናውያን ለምግብና አስፈላጊ ቁሳቁሶች ሸመታ፣ ለሕክምና፣ ለአካላዊ እንቅስቃሴ፣ ለሥራ ወይም ለትምህርት ወደ ደጅ መውጣት ይችላሉ።

ይሁንና በቫይረሱ የተያዙ ወይም ቫይረሱ ካለባቸው ሰዎች ጋር የቅርብ ግንኙነት የነበራቸው አንድ ሶስተኛ ያህሉ ነዋሪዎች በምርመራ ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸው እስኪረጋገጥ ድረስ በመኖሪያ ቤታቸው ይቆያሉ።

Amharic  news 19 July, 2020
A sign at one of the public housing towers on Racecourse Road in Flemington, Melbourne. Source: AAP

በርካታ የአልፍሬድ ጎዳና የጋርዮሽ መኖሪያ ነዋሪዎች የጤና፣ ስነ ልቦናና የሥራ ድጋፍ እንደሚሹ ተናግረዋል። 

የቪክቶሪያ ዕምባ ጠባቂ የአልፍሬድ ጎዳናና ሌሎች ስምንት የጋርዮሽ መኖሪያ ነዋሪዎችን ጨምሮ ጁላይ ውስጥ ለአምስት ቀናት ከቤት ውጪ እንዳይንቀሳቀሱ በተደረጉበት ወቅት የክብካቤ ይዘቶቹ ምን ያህል ሙሉዕ እንደነበሩ እየመረመረ ይገኛል።

ከነዋሪዎቹ ጋር በተደረጉት ንግግሮች የምግብና አስፈላጊ የሕክምና አቅርቦት፣ አካላዊ እንቅስቃሴ የማድረግ፣ የውጪ አየር ማግኘትና ክብካቤ ጉድለት ተደጋግመው ተነስተዋል።


1 min read

Published

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now