ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶችና ሴቶች ማራቶን የወርቅ ባለቤት ሆኑ

*** ለወርቅ ባለቤትነት የበቁት አትሌት ታምራት ቶላና አትሌት ጎትይቶም ገብረስላሴ ናቸው

News

Gold medalist Gotytom Gebreslase of Team Ethiopia (L), and Gold medalist Tamirat Tola of Team Ethiopia (R). Source: Getty

በኦሪጎን 18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የተወዳደሩት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በረጅም ርቀት ውድድሮች አዲስ ሬኮርድ ጭምር በማስመዘገብ  የሜዳል ባለቤቶች ለመሆን በቅዋል።

ከሰዓታት በፊት በተካሔደው የሴቶች ማራቶን ውድድር የ27 ዓመቷ አትሌት ጎትይቶም ገብረስላሴ ውድድሩን 2 ሰዓት 18 ደቂቃ ከ 11 ሰከንድ በሆነ ውጤት በአንደኛ ደረጃ ጨርሳ የወርቅ ባለቤት ሆናለች።
News
Gotytom Gebreslase of Team Ethiopia reacts as she wins gold in the Women's Marathon on day four of the World Athletics Championships Oregon22. Source: Getty
ጎትይቶም ቀደም ሲል በቶኪዮ 2022 የማራቶን ውድድር 2 ሰዓት 18 ደቂቃ ከ 18 ሰከንድ በመጨረስ ሶስተኛ ሆና የነሐስ ሜዳል ያገኘች ሲሆን፤ በ2021 በጀርመን በተካሔደው የበርሊን ማራቶን 2 ሰዓት 20 ደቂቃ ከ 09 ሰከንድ በማጠናቀቅ ለወርቅ ሜዳል በቅታለች።
News
Gotytom Gebreslase from Ethiopia smiles at the award ceremony after she was the first woman to cross the finish line after 2:20:09 hours at the Berlin Marathon. Source: Getty
ቀደም ባለው ቀንም በኦሪጎን 22 የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮን በተካሔደው የወንዶች ማራቶን የ30 ዓመቱ አትሌት ታምራት ቶላ የሻምፒዮኑን አዲስ ሬኮርድ በማስመዝገብ 2 ሰዓት 5 ደቂቃ ከ 36 ሰከንድ በማጠናቀቅ የወርቅ ሜዳል ባለቤት ሆኗል።
News
Silver medalist Mosinet Geremew of Team Ethiopia, gold medalist Tamirat Tola of Team Ethiopia and bronze medalist Bashir Abdi of Team Belgium. Source: Getty
ኢትዮጵያዊው ሞሲነት ገረመው ከታምራት 68 ሰከንዶች ተከትሎ ለብር ሜዳል በቅቷል።   

 


Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶችና ሴቶች ማራቶን የወርቅ ባለቤት ሆኑ | SBS Amharic