በዛሬው ዕለት 21 ሰዎች ቪክቶሪያ ውስጥ በኮሮናቫይረስ ሲጠቁ ሰባት ሕይወታቸውን አጥተዋል።
ሕይወታቸው ያለፈውን ሰባት ሰዎች ጨምሮ በመላው ቪክቶሪያ 757 በአገር አቀፍ ደረጃ 844 ሰዎች በቫይረሱ ሕይወታቸውን አጥተዋል።
የሜልበርን 14 ቀናት አማካይ ዕለታዊ የኮሮናቫይረስ ቁጥር 39.3 ደርሷል።
በቪክቶሪያ መንግሥት በኩል የተጣሉ የኮቨድ - 19 ገደቦችን ለማላላት የሚሻው የ14 ቀናት አማካይ የቫይረስ ተዛማችነት ቁጥር እስከ 50 የሚደርስ ነው።
ኮቨድ - 19 - ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ ውስጥ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ 602 ሰዎች በኮሮናቫይረስ ሲጠቁ 12 ሕይወታቸውን አጥተዋል።
በጠቅላላው ኢትዮጵያ ውስጥ 67 ሺህ 515 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል፤ 27 ሺህ 638 አገግመዋል፤ 38 ሺህ 803 በአሁኑ ወቅት በቫይረሱ ተጠቅተው ይገኛሉ።
በኮሮናቫይረስ ሳቢያ እስካሁን ኢትዮጵያ ውስጥ 1 ሺህ 72 ሰዎች ለሕልፈተ ሕይወት ተዳርገዋል።
ዩናይትድ ስቴትስ - ጠቅላይ ፍርድ ቤት
የዩናይትድ ስቴትስ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ የነበሩት ዝነኛዋ ሩዝ ባደር ጊንስበርግ በ87 ዓመታቸው በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
ዳኛ ጊንስበርግ በካንሰር በሽታ ለረጅም ጊዜ ታመው የነበሩ ሲሆን በአያሌ አሜሪካውያን በተለይም በሴቶች ዘንድ የዕውቀት፣ ፍትሕና የጾታ እኩልነት ተምሳሌት ሆነው ይታዩ የነበሩና የሚታሰቡ ናቸው።
የዳኛ ጊንስበርግ ተተኪ አስመልክቶ የ2020 ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ላይ ብርቱ ፖለቲካዊ ትንቅንቅ እንደሚፈጥር ይጠበቃል።

A marcher holds a sign that says "Ruth Shall Set Us Free" during the Woman's March in NY in January 2020. Source: Getty Images
Share

