ኢትዮጵያና ኬንያ ቻይና መራሽ የአፍሪካ ቀንድ የሰላም ጉባኤ ሊያስተናግዱ ነው

*** በደቡብ አውስትራሊያ ምርጫ መንግሥታቸውን ድል የተነሳው ተሰናባች የደቡብ አውስትራሊያ ፕሪሚየር ስቲቨን ማርሻል ከሊብራል ፓርቲ መሪነታቸው እንደሚለቁ አስታወቁ።

News

Kenyan President Uhuru Kenyatta and Chinese President Xi Jinping (L), and Ethiopia's Prime Minister Abiy Ahmed and Chinese President Xi Jinping (R). Source: Getty

በኢትዮጵያና ኬንያ አስተናጋጅነት ቻይና መራሽ የሰላም ጉባኤ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊካሔድ ነው።

በአፍሪካ ቀንድ ላይ የሚያተኩረው የሰላም ጉባኤ በ2022 አጋማሽ ላይ የሚካሔድ መሆኑን ባለፈው ፌብሪዋሪ የተሰየሙት የቻይና የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ሹ ቢንግ ትናንት ቅዳሜ ናይሮቢ በሚገኘው የቻይና ኤምባሲ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል። 

ልዩ ልዑኩ በአፍሪካ ቀንድና በቻይና መካከል ያለው ግንኙነት የቆየና ስትራቴጂካዊ ሽርክናን የተላበሰ መሆኑን ጠቅሰዋል። 

አያይዘውም፤ በአካባቢው የድንበር፣ የጎሣና  የሃይማኖት ግጭቶች ያሉ መሆኑን ያመላከቱት አቶ ሹ የሰላምና ፀጥታ መስፈን ጠቀሜታንም አንስተው ቻይና ልዩነቶች በምክክርና ድርድር እንዲፈታ የምትሻ መሆኑን ተናግረዋል። 

ልዩ ልዑክ ሹ ቢንግ ኤርትራ፣ ኢትዮጵያ፣ ጂቡቲ፣ ሶማሊያና ኬን ያን የጎበኙ ሲሆን፤ በቀጣይነትም ኡጋንዳና ደቡብ ሱዳንን ይጎበኛሉ። 

በሌላም በኩል፤ አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድን ጃኑዋሪ ላይ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ አድርጋ የሰየመችው ዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን "በአፍሪካ ቀንድና አካባቢው በመካሔድ ላይ ያሉት የፖለቲካ፣ ፀጥታና ሰብዓዊ ተግዳሮቶች የዩናይትድ ስቴትስን ያልተቋረጠ ትኩረት ይሻል" ብለዋል። 

 ምርጫ ደቡብ አውስትራሊያ

ተሰናባች የደቡብ አውስትራሊያ ፕሪሚየር ትናንት ቅዳሜ ማርች 19 በተካሔደው የደቡብ አውስትራሊያ ምርጫ የመንግሥታቸውን ድል መነሳት ተከትሎ ከሊብራል ፓርቲ መሪነታቸው እንደሚለቁ አስታወቁ።

አቶ ማርሻል ትናንት ማምሻውን በምርጫው በለስ ያልቀናቸው መሆኑን አስመልክተው ሲናገሩ "በምርጫው ውጤት ደስተኛ አይደለሁም። ይሁንና ሙሉ ኃላፊነትን እወስዳለሁ። የሕዝብን ፈቃድ እቀበላለሁ" ብለዋል።

አክለውም የደቡብ አውስትራሊያ 46ኛው ፕሪሚየር ሆነው ለማገልገል በመታደላቸው ትልቅ ክብር የሚሰማቸው መሆኑንና በዳንስታን ምክር ቤት አባልነታቸው በመቀጠል አገልግሎታቸውን መስጠት እንደሚሹም ገልጠዋል።

News
Outgoing South Australian Premier Steven Marshall. Source: Getty

ይሁንና የሌበር ፓርቲን ወክለው የዳንስታን ምክር ቤት ወንበር ዕጩ ሆነው ከቀረቡት ክሬሲዳ ኦሃንሎን ጋር ከሕዝብ ያገኙት ድምፅ በእጅጉ ተቀራራቢ በመሆኑ፤ ከቶውንም በሌበር ፓርቲ ተረትተው ወንበራቸውንም ሊያጡ እንደሚችሉ ግምት አለ።    

ተሰናባቹ ፕሪሚየር ፓርቲያቸው ስብሰባ አካሂዶ ተተኪያቸውን እስኪመርጥ ድረስ በአመራር ኃላፊነታቸው ይቆያሉ። 

በሌላ በኩል አዲሱ ተመራጭ የደቡብ አውስትራሊያ 47ኛ ፕሪሚየር ፒተር ማሊናዩስካስ ጤናን ማዕከል ያደረገ ሰፊ የድኅረ-ወረርሽኝ ፖሊሲ ግብር ላይ ለማዋል መወጠናቸውን አስታውቀዋል።

News
South Australia's 47th Premier Peter Malinauskas is the first to defeat an incumbent government during the pandemic. Source: AAP

አያይዘውም፤ ማንም ይመረጥ ማን ከወደፊቱ የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ተባብረው እንደሚሠሩ አመላክተዋል።

ሆኖም፤ ለደቡብ አውስትራሊያ የማይበጅ ከሆነ አሌ ሊሉ እንደሚችሉ አሳስበዋል። 

ሌበር ራሱን ችሎ አብላጫ የምክር ቤት አባላት ያሉት መንግሥት ለማቆም የሚያሻው 24 የምክር ቤት ወንበሮች ሲሆኑ 25 የተረጋገጡ 2 የማሸነፍ ተስፋ የተጣለባቸው ወንበሮችን በማግኘት 27 የምክር ቤት አባላት ያሉት መንግሥት ሊያቆም እንደሚችል ይጠበቃል።    

 


2 min read

Published

Updated

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now