የፌዴራል መንግሥቱ አውስትራሊያ ለገቡ ዩክሬናውያን ጊዜያዊ የሰብዓዊ ቪዛ ሊሰጥ ነው።
ቪዛው አውስትራሊያ የገቡ ዩክሬናውያንን ለሶስት ዓመታት የሥራ፣ የትምህርትና የሜዲኬር ግልጋሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል።
አውስትርሊያ ከ3,000 በላይ ለዩክሬይን ስደተኞች የሰብዓዊ ቪዛ ሰጥታለች።
መንግሥት ተጨማሪ ወታደራዊ እርዳታ ማድረጉንም አስታውቋል።
የሰላም ንግግር
የዩክሬይን ፕሬዚደንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ በድጋሚ "ትርጉም ያለው" የሰላም ንግግር ለማድረግ ለሩስያ ጥሪ አቀረቡ።
ሁለቱ አገራት ባለፉት ሳምንታት ከስምምነት ላይ ያላደረሱ ተከታታይ ድርድሮችን በልዑካኖቻቸው በኩል አድርገዋል።
የሩስያና ዩክሬይን ጦርነት የቀጠለ ሲሆን በዩክሬይን ማሪዩፖል ከተማ ላይ ከፍተኛ ጥቃት እየደረሰ ነው።
ፕሬዚደንት ዜሌንስኪ ዩክሬይንን ከሩስያ ወረራ እየተከላከሉ ላሉ ወታደሮች ማበረታቻ የሜዳል ሽልማቶችን ከምስጋና ጋር ሰጥተዋል።
በሌላም በኩል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በጦርነቱ ሳቢያ የ800 ሰላማዊ ሰዎች ሕይወት መቀጠፉንና 3.3 ሚሊየን ዩክሬናውያን ለስደት መዳረጋቸውን ገልጧል።

